Your cart is currently empty!
በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የተለያዩ የእርሻ መሳሪያዎችና ተቀጽላ መሳሪያዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Addis Zemen(Feb 02, 2026)
የጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን (የእርሻ መሳሪያዎች አቅርቦትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ) አዲስ አበባ የሚገኙ ከዚህ በታች የተገለጹትን የተለያዩ የእርሻ መሳሪያዎችና ተቀጽላ መሳሪያዎችን በጨረታ ቁጥር: መለዋ/01/2018 በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
|
ሎት |
የመለዋወጫዎች ዝርዝር |
የመለዋወጫዎች ብዛት በአይነት |
|
ሎት 1 |
የ YTO ትራክተር መለዋወጫዎች |
64 |
|
ሎት 2 |
የ IMT ትራክተር መለዋወጫዎች |
90 |
|
ሎት 3 |
የ ZT ትራክተር መለዋወጫዎች |
364 |
|
ሎት 4 |
የ Bellarus ትራክተር መለዋወጫዎች |
213 |
|
ሎት 5 |
የ Combinir (አጭዶ መውቂያ) መለዋወጫዎች |
274 |
|
ሎት 6 |
የተለያዩ ባልዲዊን ፊልተሮች |
63 |
|
ሎት 7 |
የተለያዩ የእርሻ መሳሪያ ተቀጽላ መለዋወጫዎች |
196 |
|
ሎት 8 |
የተለያዩ የጀነሬተር እና Standard መለዋወጫዎች |
348 |
|
ሎት 9 |
የተለያዩ ጎማዎች፣ ከመነዳሪዎችና ፍላፖች |
12 |
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ሁኔታዎች በማሟላት መወዳደር ይችላሉ።
ሀ) ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት እቃዎቹ በሚገኙበት በኮርፖሬሽኑ ዋና ጽ/ቤት አዲስ አበባ በእርሻ መሳሪያዎች አቅርቦት ዘርፍ ሽያጭ ክፍል በመቅረብ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
ለ) የጨረታ ሰነድ ሽያጭ የሚካሔደው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 የስራ ቀናት ክፍት ይሆናል፡፡ ጨረታውም በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ተዘግቶ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የእርሻ መሳሪያዎች አቅርቦትና ሽያጭ ቢሮ ይከፈታል።
ሐ) ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለጨረታ ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 3% በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ (CPO) በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የእርሻ መሳሪያዎች አቅርቦትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ (Ethiopian Agricultural Businesses Corporation Agricultural Equipment Supply and Mechanization Sector) በማዘጋጀት ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ቃሊቲ በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ ጽ/ቤት(ሳሪስ አቦ ከፋ ምግብ ኮምፕሌክስ
በስተጀርባ፣ ከደብረዘይት መንገድ 200 ሜትር ገባ ብሎ)
ስልክ ቁጥር 0114-42-25-82, 0114-40-39-70, 0114 42-34-38
የኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን