የሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ


Be’kur(Feb 02, 2026)

የሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ

የወረታ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት የከተማ ቦታ ስለመያዝ በደነገገው አዋጅ 72/2004/መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ለ1ኛ ዙር 1ኛ. ቀበሌ 01 በምስራቅ መንገድ፣ በምዕራብ አማረ መስፍን፤ በሰሜን ወረታ ትሬዲንግ አ/ማ/ር ፣በደቡብ መንገድ፣ ስፋቱ 522 ካ/ሜትር ለድርጅት አገልግሎት የሚውል 01 ቦታ፡፡ 2ኛ. ቀበሌ 01 በምስራቅ መንገድ፣ በምዕራብ መንገድ፤ በሰሜን መንገድ እና አዲሱ፣ በደቡብ ጌቴ ይጅቡ፣ስፋቱ 562.5 ካ/ሜትር ለድርጅት አገልግሎት የሚውል 01 ቦታ፡፡3ኛ. ቀበሌ 03 በምስራቅ ኑርሁ ሴን፣ በምዕራብ ሀብቴ አስካለማርያም፣ በሰሜን መንገድ ፣በደቡብ እንድሪስ፣ስፋቱ 120 ካ/ ሜትር በተራ ቁጥር 03 የተፃፈ ቦታ አሸናፊው 100 በመቶ ክፍያውን መክፈል ይኖርበታል፡፡

  1. የጨረታ ሰነድ ቢሮ ቁጥር 17 በመምጣት የማይመለስ 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይቻላል፡፡
  2. የጨረታ አይነት መደበኛ፡፡
  3. የጨረታ ሰነድ መግዣ ቀን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉበት 10 ተከታታይ የስራ ቀን ከጧቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ስዓት ብቻ ይሆናል፡፡
  4. የጨረታ ሰነድ መሸጫ ጊዜ የሚያልቀው በ10ኛው ቀን 11፡30 ነው፡፡
  5. ጨረታው የሚከፈተው በ11ኛው ቀን ወ/ከ/አስ/ከ/ል/ቤ/ኮ/ጽ/ቤት ከጥዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ጨረታው ይከፈታል፡፡
  6. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  7. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም ሲፒኦ በባንክ የተረጋገጠ የገንዘብ ክፍያ ትዕዛዝ ለድርጅቱ 15 በመቶ ለመኖሪያ 20 በመቶ በማቅረብ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የተያዘ ገንዘብ አሸናፊው ከተለየ በኋላ የሚመለስ ይሆናል፡፡
  8.  የግንባታ ደረጃ ለድርጅት
  9. የቦታው አገልግሎት በእያንዳንዱ ምድብ ከሰነዱ ጋር በሚሸጠው ሰነድ ሰንጠረዥ ላይ የተቀመጠው ይሆናል፡፡
  10.  ለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 446 00 26 ደውለው ማግኘት ይችላሉ፡፡

የወረታ ከተማ አስ/ ከተ/ል/ ቤ/ ኮን/ ጽ/ቤት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *