የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የየማነብርሃን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፣ አላቂ የፅዳት ዕቃዎች፣ ቋሚ ዕቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ እድሳትና ጥገና፣ ፕሪንተር እና ሌሎች ተዛማጅ ኤሌክትሮኒክስ መግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Feb 11, 2026)

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 001/2018

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የየማነብርሃን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

  • ሎት 1 አላቂ የቢሮ ዕቃዎች 700
  • ሎት 2 አላቂ የፅዳት ዕቃዎች 450
  • ሎት 3 ፕሪንተር እና ሌሎች ተዛማጅ ኤሌክትሮኒክስ… 1900
  • ሎት 4 ቋሚ ዕቃዎች 200
  • ሎት 5 ኤሌክትሮኒክስ እድሳትና ጥገና 580

1. በዘርፉ አግባብነት ያለው ህጋዊ የታደሰ ፈቃድ እና የዘመኑን ግብር የከፈለ።

2. በመንግሥት ግዥ ኤጀንሲ በእቃ አቅራቢነት የተመዘገበበትን ኮፒ ማቅረብ የሚችል።

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።

4. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመከፈል የጨረታውን ዝርዝር ሰነድ ከግዥ ክፍል መውሰድ ይችላሉ።

5. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በመሙላት በታሸገ ፖስታ ኦርጅናልና ኮፒ ማስገባት አለባቸው፡፡

6. ተጫራቾች ከላይ በየሎቱ የተጠቀሱትን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ለእያንዳንዱ ሎት ማስያዝ አለባቸው።

7. ናሙና ለሚያስፈልጋቸው የዕቃ አይነቶች ናሙና ማቅረብ እና በናሙና ለማቅረብ የሚያስቸግሩትን በፎቶ በማምጣት ጨረታው ከመዘጋቱ ቀደም ብለው ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ናሙና ለማይቀርብባቸው የእቃ አይነቶች በሚቀርበው የእቃ መግለጫ (specification) መሰረት መቅረብ ይኖርበታል፡፡ ናሙናዎች በጨረታው ለተሸነፉ ተጫራቾች ተመላሽ ይሆናል፡

8. ጥቃቅንና አነስተኛ እቃ አቅራቢዎች ከሚመለከተው አካል በትምህርት ቤቱ ስም የተጻፈ ደብዳቤ አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

9. አሸናፊው ያሸነፈበትን እቃ የትምህርት ቤቱ የእቃ መረከቢያ እስቶር ድረስ በራሱ ትራንስፖርት በማቅረብ ማስረከብ ይኖርበታል።

10. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስረኛው(10ኛ) ቀን በአስራ አንድ ሰአት (11፡00) ታሽጎ በአስራ አንደኛው (11ኛ)ቀን በአራት ሰዓት(4፡00) ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

11. አሸናፊው ውል ገብቶ እቃዎቹን ከማስገባቱ በፊት የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ ማስያዝ አለበት ጥቃቅንና አነስተኛ እቃ አቅራቢዎች ከሚመለከተው አካል የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- ወይራ ሰፈር አደባባይ ፊት ለፊት ገባ ብሎ

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0113696814/0113490998

በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት የየማነብርሃን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት