የፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ ሥራዎች በግራናይት በላይምስቶን እና በባዛልት ዘመኑን በዋጀ የማሽን አቀራረጽ በማስቀረፅ ለማሠራት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ ሥራዎች በግራናይት በላይምስቶን እና በባዛልት ዘመኑን በዋጀ የማሽን አቀራረጽ በማስቀረፅ ለማሠራት ይፈልጋል


Addis Zemen (Apr 12, 2026)

የጨረታማስታወቂያ  ቁጥር 001/2018

የፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አዲስ በማስገንባት ላይ ላለው የህንፃ ቤተክርሲቲያን ከዚህ በታች የተመለከቱትን ልዩ ልዩ ሥራዎች በግራናይት በላይምስቶን እና በባዛልት ዘመኑን በዋጀ የማሽን አቀራረጽ በማስቀረፅ ለማሠራት ይፈልጋል።

  • በለሰለሰ ሁኔታ የተቀረጸ የውጭ ግድግዳ ግራናይት ልባስ (ክላዲንግ)
  • የቨራንዳ አምዶች (column) የላይም ስቶን ልባስ (ከላዲንግ)
  • የመስኮት እና የበር ፍሬም (በላይምስቶን)
  •  የባዛልት ድንጋይ በቤዝ ፍሬም (ዘኮሎ)
  • የወገብ አካፋይ ፍሬም(መቀነት) በግራናይት

1. የሥራው ዘርፍ

ተጫራቾች በሚከተሉት አማራጮች ተለይተው በቀረቡ ምድቦች ላይ መወዳደር ይችላሉ፦

  • ምድብ ፦የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እና ገጠማ
  • ምድብ 2፦የገጠማ /የእጅ/ሥራ ብቻ
  • ምድብ 3፦የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ብቻ

ተጫራቾች አንድም ሆነ ከዚያ በላይ በሆኑ ምድቦች ላይ መሳተፍ ይችላሉ

2. ተጫራቾች ሲያሟሏቸው የሚገቡ መሠረታዊ መስፈርቶች

  • በዘርፉ የታደሰ የንግድና የሥራ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው ።
  • በተመሳሳይ የቤተክርስትያን ሥራዎች ላይ በቂ የሥራ ልምድ ያላቸው እና የመልካምሥራ አፈጻጸም ማስረጃቸውን በፎቶግራፍ አስደግፈው ማቅረብ የሚችሉ።
  • ሥራውን ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የድንጋይ ቅርፅ ማውጫ ማሽነሪና የወርክሾፕ አደረጃጀት ያላቸው።

3. የጨረታ ሰነድ አወሳሰድና አቀራረብ

 ተጫራቾች የማይመለስ ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን

ከቤተክርስቲያኑ የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ ጽ/ቤት ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ የስራ ቀናት መውሰድ ይችላሉ ።

  • ተጫራቾች የቴክኒክና የፋይናንስ ሰነዶቻቸውን በሁለት ቅጂዎች (አንድ ዋናና ሁለት ቅጂዎች) ለየብቻ በሰም በታሸጉ ኤንቨሎፖች ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) የጠቅላላዋጋውን 2% በሲፒኦ (CPO) ወይም በባንክዋስትና በፈረንሳይ ደብረፀሐይ ቅዱስጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ህንፃ አሰሪ ኮሚቴ ስም ማስያዝ ይኖርባቸዋል ።

4. የጨረታመዝጊያናመክፈቻ

ጨረታው ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ሰባት ተከታታይ የሥራ ቀናት ቆይቶ፣ በዚያው ቀን ከቀኑ 4፡ዐዐ ተዘግቶ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቤተክርስቲያኑ ሰበካ ጽ/ቤት ይከፈታል።

5. ልዩ ማሳሰቢያ

  • ማንኛውም ተጫራች የግንባታ ሂደት ጉብኝት (Site Visit) የማድረግ ግዴታ ያለበት ሲሆን ፣ የቴከኒክ ምዘናው ውጤታቸው ከ70% በላይ ለሆኑ ተጫራቾች ብቻ የፋይናንስ ሰነዳቸው የሚከፈት ይሆናል፡፡
  • የጨረታ ተወዳዳሪዎች የስራ ቦታ (work shop) እና የሰሩዋቸው ስራዎች በቴክኒካል ግምገማ ወቅት በጨረታ ኮሚቴ ይጎበኛሉ።
  • የቴክኒካል እና የፋይናንሻል ግምገማ ድምር ውጤት ከፍተኛ ነጥብ ያመጣ ተጫራች የጨረታው አሸናፊ ይሆናል።
  • ተጫራቾች ለናሙና የሚሆን የግራናይት ቅርፅ በደብሩ ግቢ ውስጥ ሠርተው ማሳየት ይኖርባቸዋል።
  • ቤተክርስቲያኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ አዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02

ስልክ ቁጥር 0911223523/ 0911231951

በፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ህንፃ አሰሪ ኮሚቴ


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *