የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት ለሴፍትኔት ፕሮግራም የሙያ ግንባታ ሥራ ማስፈፀሚያ ግልጋሎት የሚውል የተማሪዎች የመማሪያ ክፍል የግንባታ ሥራ በቀበሌ 06፣ የቴሌ ታወር እና የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01፣ በቪዥን ላይብረሪ የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01 በሴፍትኔት ለፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ተብሎ ከፀደቀ በጀት በሀገራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት ለሴፍትኔት ፕሮግራም የሙያ ግንባታ ሥራ ማስፈፀሚያ ግልጋሎት የሚውል የተማሪዎች የመማሪያ ክፍል የግንባታ ሥራ በቀበሌ 06፣ የቴሌ ታወር እና የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01፣ በቪዥን ላይብረሪ የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01 በሴፍትኔት ለፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ተብሎ ከፀደቀ በጀት በሀገራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል


Addis Zemen (Apr 14, 2026)

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት ለሴፍትኔት ፕሮግራም የሙያ ግንባታ ሥራ ማስፈፀሚያ ግልጋሎት የሚውል በሎት-1 የተማሪዎች የመማሪያ ክፍል የግንባታ ሥራ በቀበሌ 06 በሎት -2 የቴሌ ታወር እና የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01 በሎት-3 በቪዥን ላይብረሪ የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01 በሴፍትኔት ለፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ተብሎ ከፀደቀ በጀት በሀገራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ለምታሟሉ ባለሙያዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።

  • ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ የንግድ ምዝገባ መለያ ቁጥር /Tin No/ የዘመኑ የታደሰ የአቅራቢነት ሰርተፊኬት/በኦንላይን በፌዴራል በአቅራቢነት ዝርዝር የተመዘገበበት ማስረጃ/ የቫት ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ ጊዜው ያላለፈበት የቫት ዲክላሬሽን እና የኮንስትራክሽን የብቃት ማረጋገጫ ቅጂ ከዋናው ዶኩመንት ጋር ማቅረብ የምትችሉ።
  • ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ሚያዝያ 6 ቀን 2018 . ጀምሮ እስከ ግንቦት 5 ቀን 2018 . 11:30 ሰዓት የማይመለስ በኢትዮጵያ ገንዘብ 500.00/ አምስት መቶ ብር/ እየከፈላችሁ ከዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት በግዥ ቢሮ ቁጥር 7 የጨረታ ሰነድ መውሰድ ትችላላችሁ።
  • ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት በሎት-1 የሙያ የተማሪዎች የመማሪያ ክፍል የግንባታ ሥራ በኢትዮጵያ ገንዘብ 200000.00/ ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በሎት -2 የቴሌ ታወር እና የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ ብር 20000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ በሎት-3 በቪዥን ላይብረሪ የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ ብር 20000.00/ሃያ ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ የባንክ ክሬዲት ሌተር፣ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ አለባችሁ።
  • የጨረታ ሳጥን በከተማ ዓዲግራት ዕቅድና ፋይናንስ የሚገኝ ሲሆን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተጫራቾች ክፍት ይሆናል።
  • ጨረታው ግንቦት 7 ቀን 2018 . ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ታሽጎ በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት በዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት ተጫራቾች ወይም ወኪላቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  • የሚሞላው ዋጋ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም ስርዝ ድልዝ ካጋጠመ የባለቤቱ ፊርማ መደረግ አለበት
  • የሚሞላው ዋጋ ከነቫቱ መሆኑና አለመሆኑን ሊገለፅ ይገባል፤ ካልተገለፀ ደግሞ የተሞላው ዋጋ ግዥ ፈፃሚ አካል ከነቫቱ መሆኑን ታሳቢ ያደርጋል።
  • በእያንዳንዱ የመጫረቻ ሰነድ ማህተምና ፊርማ የባለቤቱ ተደርጎበት ቴክኒካልና ፋይናንሻሉን ተብሎ ለየብቻው ታሽጎ በሁለት ኮፒ ተደርጎ ማቅረብ አለበት።
  • መሥሪያ ቤታችን ይህ ጨረታ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ በሥራ ሰዓት በአካል ወደ ቢሯችን በመምጣት ወይም በሞባይል ቁጥር 0914 123 546 ወይ 0941 336 816 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።

ዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *