Reporter (Apr 22, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር DCDE 009/2018
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት ለድርጅቱ የጥበቃ እና ፋተሻ አገልግሎት የሚሰጡ ኤጀንሲዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የአገልግሎት ግዢ መፈፀም ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት፡–
- ተጫራቾች የዘመኑ ግብር የገበሩበትን ንግድ ፈቃድ ተ.እ.ታ (VAT) ወይም የሽያጭ ታክስ (Turn over Tax) ተመዝጋቢ ለመሆናቸው በደንቡ መሠረት ከመንግስት የግዥ ኤጀንሲ በአቅራቢነት የተመዘገቡ፣ በማንኛውም ጨረታ ለመሳተፍ የሚችል Tax Clearance እና ሌሎች ማስረጃዎች ማቅረብ አለባቸው:: በተጨማሪም በማንኛውም የመንግስት ግዥ እንዳይሳተፉ የታገዱ ድርጅቶች ዲዛይን ድርጅቱ መረጃውን ካገኘ በጨረታ እንዳይሳተፉ ወይም ከጨረታ ውጪ እንዲሆኑ ይደረጋል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዐት ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡30- 6፡30 ከሰዐት ከ7፡30-11፡00 እስከ በድርጅታችን ፋይናንስ ዴስክ 4ኛ ፎቅ መውሰድ ይችላሉ።
- የጨረታ ማስከበሪያ እንደ ተጫራቹ ምርጫ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) ወይም በባንክ የተሰጠ የተረጋገጠ ቼክ (CPO) ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ድርጅታችን ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።
- ጨረታው ከሚያዝያ 14 ቀን 2018 እስከ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት የጨረታው ሳጥን ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የመክፈቻ ስነ–ስርዓት ይካሄዳል ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በአከፋፈት ሂደት ባይገኙም የጨረታው የአከፋፈት ሂደት አያግደውም።
- የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀን ቅዳሜ እሁድ ወይም የህዝብ በአል ቀን ከሆነ ቀጣይ ወዳለው የስራ ቀን ይተላለፋል።
- የጨረታ ሰነድ ሽያጭ የማይመለስ ብር 200.00(ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ሰነዱ በድርጅታችን ፋይናንስ ዴስክ መውሰድ ይጠበቅባችኋል።
አድራሻ፡– የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት
የቀጥታ ስልክ ቁጥር 011 896 06 33/011 896 06 23
አድራሻ ካሳንቺስ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጀርባ ከዚህ ቀደም ስኳር ኮርፖሬሽን
የነበረበት የኪያ–ሜድ ኮሌጅ ህንጻ አራተኛ ፎቅ