Addis Zemen (Apr 22, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር ኢአጽ/ግንአዳ/018/2018
የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ለ2019 ዓ.ም ሥራ ዘመን የሚያገለግሉ አጀንዳዎችን እና ቀን መቁጠሪያዎችን በጨረታ አወዳድሮ ማሳተም ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
ብዛት |
|
1. |
Premium Executive Diary Gift Set |
3,000 በቁጥር |
|
2. |
Standard (Normal) mDiaries |
20,000 በቁጥር |
|
3. |
Branded Table Calendars |
20,000 በቁጥር |
ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አቅራቢዎች በጨረታው እንዲሳተፉ ተጋብዘዋል።
1- በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ ያላቸውና በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ለመመዝገባቸው ከድረገጹ (website) ዓትመው ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ ይኖርባቸዋል።
2- ተጫራቾች በተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡና የግብር መለያ ሰርተፊኬት ያላቸው መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት እና ታክስ ክሊራንስ ማቅረብ አለባቸው።
3- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለገሐር በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 ድረስ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
4- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 350,000.00 (ብር ሶስት መቶ ሃምሳ ሺ) በባንክ ክፍያ ማዘዣ (cpo) ወይም ለዘጠና ቀናት የሚቆይ ቅድመ ሁኔታ ያላስቀመጠ የባንክ ዋስትና ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
5- ተጫራቾች መወዳደሪያ ሠነዳቸውን በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ለገሐር በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በእለቱ ማለትም ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢንተርፕራይዝ አገልግሎት ጽ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ይከፈታል።
6- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
7- ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011-551 2400 የውስጥ መስመር 237/262 ወይም በቀጥታ 011-550 4931 መጠየቅ ይቻላል።
የኢትዮጵያ መድን ድርጅት