Addis Zemen (Apr 24, 2026)
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ምዕ/ኢት/ሕ/ክ/መንግስት በካፋ ዞን የአዲዮ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት 2018 በጀት ዓመት የእንስሳት መድሃኒት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በዚህ መሠረት ተጫራቾች ማሟላት የሚያስፈልጋቸው ነጥቦች
- በዘርፉ የታደሰ የሙያና ንግድ ፍቃድ ያለዉና ፎቶ ኮፒ አያይዞ ማቅረብ የሚችል
- የንግድ መለያ ቁጥር ያለውና ፎቶ ኮፒ መረጃ አያይዞ ማቅረብ የሚችል
- የጨረታ ውል ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ C.P.O ወይም ጥሬ ገንዘብ ወይም ቼክ ብር 10,000 አስር ሺህ ብር/ማስያዝ የሚችል
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ
- የሰነድ ሽያጭ የማይመለስ 300 ብር (ሦስት መቶ ብር) ብቻ መክፍል መቻል ይኖርበታል።
- ከሚያገኘው ገንዘብ 3% ለመክፈል ፍቃደኛ የሆነ
- የንግድ ምዝገባ ወረቀት ፎቶ ኮፒ አያይዞ ማቅረብ የሚችል
- የመድሃኒት አቅራቢነት ምስክር ወረቀት ያለዉና ፎቶ ኮፒ አያይዞ ማቅረብ የሚችል
- የዘመኑን ግብር ስለመከፈሉ ፎቶ ኮፒ አያይዞ ማቅረብ የሚችል
- ተጫራቾች ፋይናንሻል የጨረታ ዶክመንት ተገቢውን ሥም እና ስልክ ቁጥር በመፃፍ እና ፊርማ በማሳረፍ እንዲሁም የታደሰ መታወቂያ በማያያዝ ለየብቻ አንድ ኦሪጅናል እና ሁለት ኮፒ የተሟላ ሰነድ በተለያዩ በሰም /በሙጫ /በታሸጉ ፖስታዎች አያይዞ ማቅረብ የሚችል።
- የጨረታው ሳጥን በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲዮ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 02 ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል።
- የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።
- የተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ያለመገኘት የጨረታውን የመከፈት ሂደት አያስትጓጉልም።
- 15 ተከታታይ ቀናት የተባለው ቅዳሜና እሁድ ጨምሮ የሚቆጠር አይደለም።
- ተጫራቾች አሰሪው መ/ቤት ያዘጋጀዉን የቴክኒካል ዶከመንት መጠይቅ ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡– 0917 003 400 / 0917 335 895 / 0993 716 652 መጠየቅ ይቻላል።
በካፋ ዞን የአዲዮ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት