የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ የውሀ ማጠራቀሚያ ባለ 10,000 ሊትር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ የውሀ ማጠራቀሚያ ባለ 10,000 ሊትር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen (Apr 30, 2026)

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 141/18

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የውሀ ማጠራቀሚያ ባለ 10,000 ሊትር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ተ.ቁ

የዕቃው ዓይነት

ብዛት

የጨረታ ማስከበሪያ

የሚታሸግበት ሰዓት

የሚከፈትበት ሰዓት

1

የውሀ ማጠራቀሚያ ባለ 10000 ሊትር

11

28,000

9:00

9:05

የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፤ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸውና የቫት ተመዝጋቢነት ማስረጃዎች ያላቸውና የሚያቀርቡ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።

  • ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ለ45 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል።
  • በተጫራቾች የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ፣ በጥሬ ገንዘብ ያስያዙበትን ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
  • ተጫራቾች በቢሮው የተዘጋጀውን መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን 22/08/2018 ዓ.ም ጀምሮ የማይመለስ ብር 200 ፤ ለሰነዱ በመክፈል በከምባታ ዞን ዱራሜ ከተማ በሚገኘው የግብርና ቢሮ ቢሮ ቁጥር 03 ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ። ተጫራቾች የመጫረቻት ሠነድ ኘሮፎርማ በመሙላት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 03/09/ 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት 9፡00 ሰዓት ድረስ ቴክኒካልና ፋይናንሻል የመጫረቻ ሠነዶችን በአንድ ፖስታ በማዘጋጀት ዱረሜ ከተማ በሚገኘው የግብርና ቢሮ ቁጥር 03 ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
  • ቢሮው በቀረበው ጨረታ ላይ ከአሸናፊው ድርጅት ጋር ውል ከመፈራረሙ በፊት የግዥውን 20 ፐርሰንት መቀነስ ወይም መጨመር ይችላል።
  • የጨረታ ሳጥን 03/09/2018 ዓ/ም 9፡00 ታሽጎ 9፡05 ተጫራቾች ወይም ተወካዮቻቸው በተገኙበት የግብርና ቢሮ ቁጥር ቢሮ ቁጥር 3 ይከፈታል።
  • ቢሮው ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለበለጠ መረጃ 046-554-1461 ይጠቀሙ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *