Addis Zemen (Apr 30, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር AAPC NCB 008/2018 ዓ/ም
የአ/አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልግ
|
ሎት |
የጨረታ ዓይነት |
የናሙና መለያ |
የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ መጠን |
|
|
001 |
የኤሌክትሪክ ገመድ ግዥ |
በተቋሙ ስፔስፌኬሽን መሰረት |
15,000 |
00 |
|
002 |
የኤሌክትሮኒክስ መጠገኛ መሳሪያዎች ግዥ |
በተቋሙ ስፔስፌኬሽን መሰረት |
20,000 |
00 |
|
003 |
የፎቶ ግራፍ ማተሚያ ማሽን ግዥ |
በተቋሙ ስፔስፌኬሽን መሰረት |
300,000 |
00 |
|
004 |
የሰነድ መያዣ ቆዳ ቦርሳ |
በተቋሙ ፍላጎት መሰረት (ናሙና የሚቀርብበት) |
15,000 |
00 |
ስለዚህ፡-ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው
1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን እና በዘርፉ የተሰማሩ ለመሆናቸው በጀርባው ይመልከቱ የሚል ፅሁፍ በግልፅ ማቅረብ አለባቸው፡
2. ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
3. የታደሰ የዘመኑን ንግድ ፍቃድ እና የታደሠ ንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት መቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
4. የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው።
5. በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ክሊራንስ ማቅረብ አለበት።
6. አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ አይቻልም።
7. በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታ ውጤቱ እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን በሎቱ ፊት ለፊት የተቀመጠውን የገንዘብ መጠን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
8. ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነዶችንና የዋጋ ማቅረቢያዎችን ፋይናሻል/ሰነዶች በተለያየ ፖስታ ታሽጎ ለየብቻ መቅረብ አለባቸው።
9. ማንኛውንም ተጫራቾች የሚያስገባው ሰነድ ፋይናሻል እና ቴክኒካል የጨረታ ሰነድ አንድ ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ በፖስታው ላይ የጨረታ ሰነዱን ቁጥር የሚጫረትበትን ዕቃ አይነት በትክክል መፃፍ እንዲሁም በፖስታው ላይ ማህተም በመምታት ማስገባት ያለበት ሲሆን ፣ሰረዝ ድልዝ በፍሉድ የጠፋ ሰነድ ዋጋ ያልተሞላበት ዝርዝር ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እናሳውቃለን።
10. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያሲዙት ሲ.ፒ.ኦ. ከቴክኒክ ሰነዶች ጋር በአንድ ላይ ታሽገው መቅረብ አለባቸው።
11. በጨረታ አሸናፊ የሆኑ ድርጅቶች ዕቃውን ወይም አገልግሎቱን በራሳቸው ትራንስፖርት አ/አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ግምጃ ቤት ወይም በክፍል 6 በፍላጎት መግለጫው በተጠቀሰው የማስረከቢያ ቦታ ድረስ በማምጣት ማስረከብ አለባቸው፣
12. በጨረታ ሰነድ በክፍል 6 ውስጥ በሚገኘው የፍላጎት መግለጫ ላይ በሚገለፀው መሰረት ጨረታ ሰነዱ ላይ በቀረበው መሰረት ናሙና ማቅረብ አለበት።
13. ተጫራቾች ያቀረቡት ናሙናም ሆነ አሸናፊ መሆናቸው ሲረጋገጥ ያቀርቡአቸው ዕቃዎች ተቋሙ ባወጣው ፍላጎት መግለጫ /specifications/ መሰረት መሆኑን በቋሙ የጥራት ኮሚቴ ወይም በኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ኤጀንሲ አማካኝነት የሚረጋገጥ ይሆናል።
14. ተጫራቾች አራዳ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ከፍ ብሎ በሚገኘው የኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት 5ኛ ፎቅ ግዢ ጽ/ቤት ቢሮ ቀርበው በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፣
15. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 10 የስራ ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ እንዲሁም በማግስቱ በ11ኛው ቀን እስከ ጠዋት 4፡30 ሠዓት ድረስ ጨረታው ክፍት ሆኖ ስለሚቆይ በተቋሙ ግዢና ፋይናንስ 5ኛ ፎቅ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
16. በጨረታ ሰነዱ ክፍል 2 ላይ በሚጠቀሰው ቀን ከጠዋት 4፡30 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ 5፡00 ሰዓት ሲሆን በመ/ቤቱ 5ኛ ፎቅ ትንሹ አዳራሽ ቢሮ ቁጥር 512 ይከፈታል፣
17. ዘግይተው የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም።
18. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስ/ቁጥ- 011 862-5800 (011 111 0448)
የአ/አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ