Addis Zemen (May 09, 2026)
የተስያዩ የደንብ ልብስ ቁሳቁሶች ግዥ
ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 422/18
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የሚውል የተለያዩ የደንብ ልብስ አይነቶችን ግዥ በግልጽ ጨረታ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ በተዘረዘረው መሰረት በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ተ/ቁ |
የዕቃው አይነት |
ብዛት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የሚታሸግበት ሰዓት |
ሰነዱ የሚገኝበት ቦታ |
|
1 |
የተለያዩ ብዛት ያላቸው ደንብ ልብስ ዕቃዎች |
ብዛታቸውን በሚሸጠው ሰነድ ውስጥ ይገኛል |
50,000 |
በ16ኛው ቀን በ4፡00 ታሽጎ በዕለቱ 4፡30 ይከፈታል |
ደ/ኢ/ግ/ቢሮ ዲላ መምህራን ኮሌጅ ግቢ |
በንግድ ስራ ዘርፍ የታደሰ ፍቃድ የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸውና የቫት ተመዝጋቢነት ማስረጃዎች ያላቸውና የሚያቀርቡ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ለ60 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል፡፡
- በተጫራቾች የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ሲ–ፒ–ኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ያሲያዙበትን ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በቢሮ የተዘጋጀውን መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው ተከታታይ እስከ 16ኛ ቀን 11፡30 ድረስ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል በዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ መምህራን ኮሌጅ ግቢ ከሚገኘው የግብርና ቢሮ ግዥ ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ከፍል መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ በመሙላት ይህ የጨረታ የቴክኒካልና ፋይናሻል ኦርጅናልና ኮፒ የማጫረቻ ሰነዶች በአንድ ፖስታ በማዘጋጀት በ16 ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት በቢሮ ግዥ ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል፡፡ እንዲሁም የጨረታው ሳጥን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ 4፡10 ተጫራቾች (ተወካዮቻቸው) በተገኙበት በቢሮው የግዥ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ከፍል ይከፈታል፡፡
- ከ200,000 ሺህ ብር በላይ ለሆነ ግዥዎች ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
- ቢሮው በቀረበው ጨረታ ላይ ካሸናፊው ድርጅት ጋር ውል ከመፈራረሙ በፊት የግዥውን 20% ፐርሰንት መቀነስ ወይም መጨመር ይችላል፡፡
- የጨረታው ሳጥን መክፈቻ በ16ኛው ቀን የመንግስት የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በቀጣይ ባለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ሁለት ተወዳዳሪዎች ያቀረቡት ዋጋቸው እኩል በሚሆንበት ወቅት በእጣ የሚለይ ይሆናል፡፡
- ቢሮው ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰርዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ 046-131–0134 ይጠቀሙ፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ግብርና ቢሮ