Addis Zemen (Jun 01, 2026)
ብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምሥራቅ ሲዳማ ዞን ጭሬ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት ለ2018 በጀት ዓመት ለሴክተር መ/ቤቶች ኤሌክትሮኒክስ ዕቃ ሕጋዊ ተጫራቾችን አወዳድሮ ዕቃ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መሰፈርቶች ሟሟላት የሚችሉ ተጫራቾች በሙሉ እንዲሳተፉ እንጋብዛለን፡፡
1. በዘርፉ ቀጥተኛ የንግድ ፍቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያለው
2. የዘመኑን ግብር የከፈሉና ፍቃዳቸውን በበጀት ዓመቱ ያሳደሱ
3. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዘጋቢ የሆኑና ወርኃዊ/VAT/ሪፖርት ማቅረብ የሚችሉ
4. ለአቅራቢነት የተመዘገቡና መልካም ሥራ አፈፃፀም ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
5. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 10000/አስር ሺህ/ብር የጭሬ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት ስም በባንክ የተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ/C.P.O/ወይም ባንክ ዋስትና በማሰራት ማስገባት የሚችሉ
6. አሸናፍ የሆኑ ድርጅቶች በቂ ዋስትና ማቅረብ የሚችሉ
7. በገባው ውል መሠረት ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ ዕቃ ማቅረብና ቅድመ ናሙና ማሳየት የሚችል ተጫራች ለጨረታ የተዘጋጀው ሰነድ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቅ ሲዳማ ዞን ጭሬ ወረዳ ገቢዎች ባለሥልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ውስጥ ጨረታ ሰነድ ከያዘው ባለሙያ እጅ ሰነዱን ብር 300/ሶሰት መቶ ብር ብቻ በመከፈል ሰነዱን መወሰድ ይችላሉ፤ ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 9ቀናት በአካል በመቅረብ የጨረታ ሰነድ መወሰድ የሚችሉ መሆኑን እያሳወቅን፡ በ10ኛው ቀን ከቀኑ በ6፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች /ሕጋዊ ወክሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
8. ኦርጅናል እና ፎቶ ኮፕ ላይ ህጋዊ ማህተም በስም የታሸገ ፖስታ እንድታስገቡ እናሳሰባለን
9. አሸናፊ ድርጅት ያሸነፈበት ዕቃዎች በትከክል የጥራት ደረጃ የጠበቀ ዕቃ በማቅረብ ሲዳማ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ምሥ/ሲ/ዞ/ጭ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ድረስ ማስረከባቸው እንደተረጋገጠ ክፍያው ወዲያ ይፈጽማል፡፡
ማሳሰቢያ፡–
1. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፍልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
2. ጨረታው የሚከፈትበት የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡– 0910 740 670 / 0926 064 520
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምሥራቅ ሲዳማ ዞን ጭሬ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት