Addis Zemen (Jun 02, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር AAPC NCB 0012/2018 ዓ/ም
የአ/አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና ዕቃዎችን በግልዕ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
|
ሎት |
የዕቃው ዓይነት |
የናሙና መለያ |
የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ መጠን |
|
|
001 |
የተለያዩ ተሸከርካሪዎች ግዥ |
በተቋሙ ስፔስፊኬሽን መሰረት |
500,000 |
00 |
|
002 |
አጥንት የለሌው የበሬ ስጋ ግዥ |
በተቋሙ ፍላጎት መሰረት |
150,000 |
00 |
|
003 |
የህክምና ዕቃዎች (ማቴሪያል) ግዥ |
በተቋሙ ስፔስፊኬሽን መሰረት |
300,000 |
00 |
ስለዚህ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው::
1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን እና በዘርፉ የተሰማሩ ስለመሆናቸው በጀርባው ይመልከቱ የሚል ፅሑፍ በግል ማቅረብ አለባቸው።
2 ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
3. የታደሰ የዘመኑን የንግድ ፍቃድ እና ንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት መቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው::
4. የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው።
5. በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ክሊራንስ ማቅረብ አለበት፡፡
6. አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ አይቻልም፡፡
7. በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታ ውጤቱ እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን በሎቱ ፊት ለፊት የተቀመጠውን የገንዘብ መጠን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ተብሎ በተዘጋጀው ከባንከ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
8. ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነዶችንና የዋጋ ማቅረቢያዎችን /ፋይናንሻል, ሰነዶች በተለያየ ፖስታ ታሽጎ ለየብቻ መቅረብ አለባቸው፡፡
9. ማንኛውም ተጫራች የሚያስገባው ሰነድ ፋይናንሻልእና ቴከኒካል የጨረታ ሰነድ አንድ ኦሪጅናልና ሰነድ ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ በፖስታው ላይ የጨረታ ሰነዱን ቁጥር የሚጫረትበትን ዕቃ አይነት በትከክል መፃፍ እንዲሁም በፖስታ ላይ ማህተም በመምታት ማስገባት ያለበት ሲሆን ሰርዝ ድልዝ በፍሉድ የጠፋ ሰነድ ዋጋ ያልተሞላበት ዝርዝር ቀባይነት የሌለው መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
10 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያሲዙት ሲፒኦ ከቴክኒክ ሰነዶችጋር በአንድ ላይ አሸገው መቅረብ አለባቸው ::
11. በጨረታ አሸናፊ የሆኑ ድርጅቶች ዕቃውን ወይም አገልግሎቱን በራሳቸው ትራንስፖርት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ግምጃ ቤት ወይም በክፍል 6 በፍላጎት መግለጫው በተጠቀሰው የማስረከቢያ ቦታ ድረስ በማምጣት ማስረከብ አለባቸው።
12. በጨረታ ሰነድ በክፍል 6 ውስጥ በሚገኘው የፍላጎት መግለጫ ላይ በሚገለፀው መሰረት ጨረታ ሰነዱ ላይ በቀረበው መሰረት ናሙና ማቅረብ አለበት።
13. ተጫራቾች ያቀረቡት ናሙናም ሆነ አሸናፊ መሆናቸው ሲረጋገጥ ያቀርቡአቸው ዕቃዎች ተቋሙ ባወጣው ፍላጎት መግለጫ /specification/ መሰረት መሆኑን በተቋሙ የጥራት ኮሚቴ ወይም በሚመለከተው አካል አማካኝነት የሚረጋገጥ ይሆናል።
14 ተጫራቾች አራዳ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ከፍ ብሎ በሚገኘው የኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት 5ኛ ፎቅ ግዥ ጽ/ቤት ቢሮ ቀርቦ በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
15. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከጠዋቱ 2:30 እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ እንዲሁም በማግስቱ 11ኛው ቀን እስከ ጠዋት 4:30 ሰዓት ድረስ ጨረታው ከፍት ሆኖ በተቋሙ ግዢና ፋይናንስ 5ኛ ፎቅ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
16 በጨረታ ሰነዱ ከፍል 2 ላይ በሚጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ 5፡00 ሰዓት ሲሆን በመ/ቤቱ 5ኛ ፎቅ ትንሽ አዳራሽ ቢሮ ቁጥር 512 ይከፈታል፡፡
17. ዘግይተው የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፡፡
18. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስ/ቁጥር፦ 011862-58-00(0111110448) የአ/አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ
የአ/አበባ ፖሊስ