Addis Zemen (Jun 30, 2026)
የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
በአፈፃፀም ከሳሽ አቶ ኤሊያስ ሞጆ እና በአፈፃፀም ተከሳሽ አቶ ብርሃኑ ታደሰ ሻመሮ መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ በሀዋሳ ከተማ መናኸሪያ ክ/ከተማ ሚሊኒየም ቀበሌ ውስጥ በአፈፃፀም ተከሳሽ አቶ ብርሃኑ ታደሰ ሻመሮ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ የቦታ መለያ ቁጥር SN001010608125 የቦታ ስፋት 350.75 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመና/ክ/ከ/ልማትና ኮ/ን/ጽ/ቤት በላኩት መነሻግምት ዋጋ ብር 9,977,497.44 (ዘጠኝሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰባ ሰባት ሺህ አራት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከአርባ አራት ሳንቲም) ሆኖ በሐራጅ እንዲሸጥ እና የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ 24/10/2018ዓ/ም ጀምሮ እስከ 24/11/2018ዓ/ም ለ30 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ ውሎ የሀራጅ ሽያጩ በ25/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በግልጽ በሐራጅ እንዲሸጥ ተወስኗል።
ስለሆነም፦
- በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች/ ሕጋዊ ወኪሎች ለጨረታው ማስከበሪያ የመነሻ ዋጋውን 1/4ኛ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ተኛ ፎቅ ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 030 በአካል ቀርባችሁ በማስያዝ እና ያስያዛችሁበትን ሕጋዊ ደረሰኝ ይዛችሁ በመቅረብ ጨረታውን መሳተፍ ትችላላችሁ።
- በጨረታው ለተሸነፈ ተጫራች ለጨረታው ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ወዲያውኑ ይመለስለታል።
- ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች ያሸነፈበትን የጨረታ ገንዘብ በ15 ቀናት ውስጥ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል።
- ያሸነፈበትን የጨረታ ገንዘብ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ገቢ ካላደረገ ያስያዘው ገንዘብ ለመንግስት ገቢ ሆኖ በድጋሚ ማስታወቂያ ወጥቶ ጨረታ ይካሔድበታል።
- ጨረታውን አሸንፎ የገዛ ተጫራች የስም ዝውውር በፍ/ቤቱ ትእዛዝ ይፈጸምለታል።
- የጨረታው ሒደት የሚካሔደው 25/11/2018 ዓ/ም 4፡00-6፡00 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ከተማ መናኸሪያ ክ/ከተማ ሚሊኒየም ቀበሌ ውስጥ በአፈፃፀም ተከሳሽ አቶ ብርሃኑ ታደሰ ሻመሮ ስም ተመዝግቦ የሚታወቀው የመኖሪያ ቤት የሚገኝ ቅጥር ግቢ እንደሆነ አውቀው በተባለው ጊዜ እንድትገኙ ፍ/ቤቱ አዟል።
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት