Addis Zemen (Jul 10, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር MSF/LP/10/2026
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ከዚህ በታች የተገለፁትን የእርሻ ትራክተር እና የእርሻ አፈር መከስከሻ ተቀፅላ መሳሪያዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡
- ጥቅል አንድ፡– New Haulage Tractor
- ጥቅል ሁለት – New Harrower Implement
በመሆኑም ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
1. ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን የሀገር ውስጥ ገቢ ገብር አጠናቀው የከፈሉና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
2. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች ለእያንዳንዱ ጥቅል የማይመለስ ብር 400 (አራት መቶ ብር) በመከፈል ዘወትር በሥራ ሠዓት ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ህንፃ ግዥ ቡድን 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 215 የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ ገዝተው በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ሲገዙ የንግድ ፈቃድ ይዘው መቅረብ ይኖርባችዋል፡፡
4. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት ሠነድ ጋር የታደሰ የንግድ ፈቃድ የአቅራቢዎች የምዝገባ ሠርተፍኬት እና ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለጥቅል አንድ ብር 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) እንዲሁም ለጥቅል ሁለት ብር 150,000.00 (አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ) በሲ.ፒ.ኦ /C.P.O/ ወይም የባንክ ዋስትና /Bid bond guarantee/ በሲ.ፒ.ኦ ማቅረብ አለባቸው ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በራሳቸው የዋጋ ማቅረቢያ (Proforma invoice) ላይ በማዘጋጀት በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ እ.አ.አ. ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ሜክሲኮ ፊሊፕስ ሕንጻ ቢሮ ቁጥር 119 ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
5. ጨረታው በዕለቱ ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ቢሮ ቁጥር 119 ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ::
6. ፋብሪካው ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ስልክ ቁጥር፡-0115 505 607, 0115 505 633
ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ሕንፃ
አዲስ አበባ
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ