Addis Zemen (Jul 11, 2026)
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 1
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን የባቲ ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በ2019 በጀት አመት ለባቲ ወረዳ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል
- ምድብ 1፣ አመታዊ የመኪና መለዋወጫ
- ምድብ2፤የመኪና ጎማ
- ምድብ3፤ በኪሎ ሜትር የሚቀየሩ የመኪና መለዋወጫ
- ምድብ4፤ አመታዊ የመኪና ጌጣጌጥ እቃዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ
የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ የተጠቀሱትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ከሰነዶቻቸውጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የገንዘብ መጠኑ ከ200000 /ሁለት መቶ ሺ/ ብር በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርበታል።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በሁለት ቅጂዎች ማለትም ኮፒና ኦርጂናል በማለየት በጥንቃቄ በታሸገ ኤንቨሎፕ ባቲ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በግዥ ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው።
- ተጫራቾች በሚወዳደሩበት ዘርፍ በዘመኑ የታደሰየንግድ ፍቃድ ፣የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ጨረታ ለምድብ1፤ለተገለጸው ብር 50,000.00/አምሳ ሺህ ብር/ ለምድብ2፤ ብር 25000.00 ለምድብ3፤ 6000.00 ለምድብ4፤ 3000.00 በባንክ በተረጋገጠ CPO ወይም በገቢ መቀቢያ ደረሰኝ በባቲ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ስም በምርጫቸው በአንዱ ከዋናው ኦሪጅናል የመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ እና የተጫራቾች መመሪያ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበትን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 15ኛው ቀን በባቲ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 400/አራት መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሀሳባቸውን ዋናና ቅጂ /Orignal and Copy/ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታው ታትሞ ከወጣበት ቀን ከ4/11/2018 ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ማለትም እስከ 19/11/2018 ቀን 3፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በባቲ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤትማስገባት ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ 4፡00 ሰዓት በግልጽ ይከፈታል።
- ግዥ ፈጻሚ መ/ቤት ጨረታውን በጥቅል ዋጋ /ሎት የሚያወዳድር መሆኑንና ሙሉ የጨረታ ሰነድ ዋጋ ያልሞላ ከጨረታ ውድድር ውጭ የሚሆን መሆኑንእናሳውቃለን።
- ተጫራቾት በሰነዱ ላይ ስም፣ ማህተምና ፊርማ አሟልተው መገኘት አለባቸው፤ ስርዝ ድልዝ ካለው ከውድድር ውጪ ይሆናል።
- የጨረታ ውጤት ለአሸናፊ ድርጅቶች በአድራሻ ለተሸናፊዎች ደግሞ በግልባጭ በደብዳቤና በጽ/ቤቱ የውስጥ ማስታወቂያ የምናሳውቅ ይሆናል።
- ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ላይ ተመስርተው የመወዳደሪያ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም።
- ጽ/ቤቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስለጨረታው የበለጠ መረጃ ማግኘት ከፈለጉ በባቲ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥ ንብረት አስ/ር ቡድን በአካል ቀርበው ወይም በስ.ቁ 0335532123 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ ::
ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ቦታው ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሞ ብሄረሰብ
ዞን አስተዳደር የባቲ ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት