Addis Zemen (Jul 20, 2026)
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2019
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የበረኸት ወረዳ ገንዘብ ፅ/ቤት ለሴ/መ/ ቤቶች አገልግሎት የሚውል የቧንቧ እና የውሀ መገጣጠሚያ እቃዎችን በዋን ዋሽ በጀት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል::
1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው::
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው::
3. የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸዉ፡፡
4 የተጨማሪ እሴት ታክስ VAT ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
6. የሚገዙ ዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ/ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ብቻ በመክፈል ከግ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮቁጥር4 ማግኘት ይቻላል፡፡
8.ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድቦንድ ለሚወዳደሩበት ለቧንቧና የውሀ መገጣጠሚያ እቃዎች 20,000 ሀያ ሺህ/ ብር በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲ.ፒ.ኦ/ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
9.ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋና/ኦሪጂናል እና ቅጂኮፒ/ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ቀን 28/11/2018ዓ.ም ጠዋት 3፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሀላፊ ክፍል በቢሮ ቁጥር1 በቀን 28/11/2018 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
11.ተጫራቹ የዕቃውን ዝርዝር መግለጫ ስፕስኬሽን በማሟላት ዕቃው የተመረተበትን ሀገር፣ የአምራቹን ስም የዕቃውን ሞዴልና የመሳሰሉትን አካቶ መሙላት ይጠበቅበታል፡፡
12. መ/ቤቱ ጨረታውን በሎት ድምር ዋጋ ወይም በነጠላ ዋጋ የሚያወዳድር መሆኑን ይገልፃል፡፡
13.በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 4 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 022 472 0080 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
14.መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የበረኸት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት