የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቦታ ስፋት 200 ካሬ ሜትር G+3 የሆነ ቤት መሸጥ ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቦታ ስፋት 200 ካሬ ሜትር G+3 የሆነ ቤት መሸጥ ይፈልጋል


Addis Zemen (Jul 21, 2026)

የአንደኛ ደረጃ የሐራጅ ማስታወቂያ

የአፈ ከሳሽ…………. አቶ /ሚካኤል ዮሐንስ

የአፈ/ተከሳሽ……አቶ ግርማ ስዩም

መካከል ስላለው የአፈጻፀም ክርክር ክስ ጉዳይ የማዕ/ጎን/ዞን ከፍ//ቤት የሰኔ 29 ቀን 2018 . በዋለው ችሎት በሰጠው ትእዛዝ መሰረት ምክንያት በጎንደር ከተማ በማራኪ ክፍለ ከተማ በአፈጻፀም ተከሳሽ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ በቁራሽ መሬት ምዝገባ ቁጥር AM 00205251009 የቦታ ስፋት 200 ካሬ ሜትር G+3 የሆነ በአዋሳኝ፤

  • በምስራቅ……. መንገድ…….…….…….በምእራብ……. AM 002052510010
  • በሰሜን ……. AM 00205251008….በደቡብመንገድ የሚያዋስነው ቤትና ቦታ

በመነሻ ዋጋ 24,333,360.78 ( ሃያ አራት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሰላሳ ሶስት ሺህ ሶስት መቶ ስልሳ ብር ከሰባ ስምንት ሳንቲም / በሆነ መነሻ ዋጋ በግልጽ ጨረታ እንዲሸጥ የአንደኛ ደረጃ የሐራጅ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከሐምሌ 14 ቀን 2018 . እስከ ነሐሴ 14 ቀን 2018 . ማስታወቂያው አየር ላይ ይውላል።

ከላይ በአዋሳኝ የተጠቀሰውን የድርጅት ቤት እና ቦታ መጫረት (መግዛት) የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ሁሉ ነሐሴ 15 ቀን 2018 . ከጠዋቱ 300 እስከ ቀኑ 700 ሰዓት ድረስ ቤቱ ከሚገኝበት ቦታ ድረስ በመቅረብ ቤትና ቦታውን አይቶ መጫረት እና መግዛት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች እንድታሟሉ እንገልጻለን።

  1. ቤትና ቦታው የድርጅት መሆኑን ተጫራች ማወቅ አለባቸው።
  2. ጨረታው ከሐምሌ 14 ቀን 2018 . እስከ ነሐሴ 14 ቀን 2018 . ድረስ በአየር ላይ ይውላል።
  3. ተወዳዳሪዎች ከጠዋቱ 300 ሰዓት እሰከ ቀኑ 700 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ቤቱን እና ቦታውን አይቶ መቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  4. ገዥ ሲያሸንፍ አንድ አራተኛውን ወዲያውኑ ያስይዛል።
  5. ገዥ ሲያሸንፍ 15 ቀን ውስጥ አጠቃሎ ከከፈለ ስመንብረቱ ወዲያውኑ እንዲዛወርለት ይደረጋል።
  6. የጨረታ ተወዳዳሪዎች በጨረታ ወቅት መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
  7. በጨረታ የሚወዳደሩ ራሳቸው ወይም ህጋዊ ወኪላቸው ይሆናል።
  8. በጨረታ ወቅት ሁከት የሚፈጥር በህግ ይጠየቃል።ስመንብረት ማዛዎሪያ በጨረታ አሸናፊው የሚሸፈን ይሆናል።
  9. ጨረታው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐራጅ ባይ የሚመራ ይሆናል።

ከዚህ በላይ በዝርዝር የቀረበውን የጨረታ ጥሪ ማስታወቂያ አሟልታችሁ ለመወዳደር የምትፈልጉ ሁሉ ቤቱ ከሚገኝበት ጎንደር ማራኪ ክፍለ ከተማ ቤቱንና ቦታውን በአካል ቀርበው በማየት በጨረታው ቀን እና ሰዓት በመገኘት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *