Be'kur (Jul 20, 2026)
የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ
በአፈ/ከሳሽ ካሳሁን አዳሙ እና በአፈ/ተከሳሽ እነ አቡየ ቢተው መካከል ስላለው የገንዘብ ክስ ክርክር ጉዳይ በቲሊሊ ከተማ 02 ቀበሌ በምሥራቅ ወንዴ ገ/መድን፣ በምዕራብ መንገድ፣ በሰሜን ስመኝ ጌታቸው እንዲሁም በደቡብ መዳኒት በሬ የሚያዋስነው በአፈ/ተከሳሽ አቶ አብየ ቢተው ስም ተመዝግቦ የሚገኝ የመኖሪያ ቤት መነሻ ዋጋ ሳይጠብቅ ጨረታው ከሐምሌ 13/2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ 30 ቀናት በጋዜጣ ወጥቶ ቆይቶ ጨረታው ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ባለው ጊዜ እንዲጫረት ሲል ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች ወደ ጨረታው ስትመጡ የጨረታውን መነሻ ዋጋ 1/4 ኛውን በሲፒኦ ይዛችሁ እንድትቀርቡ እናሳስባለን፡፡
የባንጃ ወረዳ ፍ/ቤት