Addis Zemen (Aug 11, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ለ2019 በጀት ዓመት የተለያዩ ቋሚና አላቂ የቢሮ እቃዎች የጽዳትና የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የኮምፒተር፡ የፕሪንተር ቀለሞችና የደንብ፣ ልብስ የቢሮ የአዳራሽ ወንበሮች በግልጽ ጨረታ ከ6211፡ 6212፡ 6218፡ 6219፡ 6313 በነጠለ ዋጋ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። ስለዚህ የሚከተሉትን የጨረታ መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል።
1 ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ኖሮአቸዉ በገንዘብ ኢኮኖሚ ልማት ትብብር ሚኒስቴር በዕቃ አቅራቢነት የተመዘገቡበትን የምስክር ወረቀት ያላቸዉ በቫት የተመዘገቡና የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
2. የሚጫረቱበትን የእቃ ዓይነት በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለጸዉን የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20000.00 /ሃያ ሺህ ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) በወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ስም ማስያዝ አለባቸዉ ወይም በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበር የተደራጁ ከሆነ ከአደራጃቸዉ አካል የዋስትና ደብዳቤ ለፍርድ ቤቱ በአድራሻ ተጽፈዉ ዋናውን ማቅረብ አለባቸዉ። ሆኖም አዲስ ከተደራጁ ዉጪ ነባሮች ሲፒኦ (CPO) የማስያዝ ግዴታ አለባቸዉ።
3. አሸናፊ ተጫራቾች ዉል ሲፈራረሙ የመልካም ስራ አፈጻጸም ዋስትና 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራቾች የጨረታዉን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 800 (ስምንት መቶ ብር) በመክፈል ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 25 መግዛት ይችላሉ።
5. ተጫራቾች የጨረታዉን ሰነድ አንድ ዋና እና ኮፒ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማቅረብ እስከ 16ኛዉ ቀን ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ዉስጥ ማሰገባት ይኖርባቸዋል። በዚሁ ቀን በ7፡30 ተዘግቶ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። እለቱ በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ጨረታዉ ይከፈታል። ለተሸነፉት ተጫራቾች ወዲያዉኑ ያስያዙት ሲፒኦ (CPO) ይመለስላቸዋል።
6. ተጫራቾች የተወዳደሩበትን የእቃ ሳምፕል ናሙና ጨረታው ከመከፈቱ ከ 1ቀን በፊት ማቅረብ አለባቸዉ።
7. ተጫራቾች በባለፈዉ ጨረታ አሸንፈዉ የአሸነፉበትን እቃ በተለያየ ምክኒያት ለፅ/ቤታችን ማቅረብ ያልቻሉ በጨረታዉ አይሳትፋም።
8. ማንኛዉም ተጫራች በሌላዉ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም።
9. መ/ቤቱ እቃዎቹን በብዛት የመጨመርም ሆነ የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።
10. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን እቃ የወረዳዉ ፍርድ/ቤት ቢሮ ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
11. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።
ማሳሰቢያ፡– አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን እቃዎች በ30 የስራ ቀናት ዉስጥ አጠናቀዉ ማስገባት አለባቸዉ።
አድራሻ፡– ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ሆለታ ከተማ ከአዲስ አበባ በአምቦ መስመር በ28 ኪ.ሜ.ላይ ይገኛል።
ስልክ ቁጥር +251 11 237 0054 +251 11 237 0530 +251 91 468 8252
በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን
የወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት