Addis Zemen (Aug 17, 2026)
ለ3ኛ ጊዜ የወጣ የሠራተኞች ደንብ ልብስ
የጨረታ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልድንግስ የገነት ሆቴል አስተዳደር ለሆቴሉ ሠራተኞች የደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- የ2018 ዓ.ም ዘመን የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት (VAT) ያለው፤
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN Number) ያለው
- በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የታክሰ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችል፤
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ሃያ ሺህ ብር (20,000) በባንክ በተረጋገጠ ሰፒዬ “ለገነት ሆቴል” በሚል በማሰራት ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ለብቻው በፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ስለጨረታው ሙሉ ዝርዝር ሁኔታ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር በ10 ተከታታይ ቀናት ጊዜ ውስጥ ከድርጅታችን የፋይናንስ ክፍል የማይመለስ 500 (አምስት መቶ ብር) በመግዛት መውስድ ይችላሉ።
- ጨረታው በአየር ላይ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉ 10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የምታቀርቡት ዋጋ በሰነዱ ላይ በግልጽ ካልተቀመጠ በስተቀር ተጨማሪ እሴት ታከስን እንደሚጨምር ተደርጎ ይወሰዳል።
- ተጫራቾች የቴክኒክ እና የፋይናንስ ሰነድ ለየብቻ በስም በታሸገ ፖስታ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ ገነት ሆቴል አስተዳደር ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው ተጫራጮች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ10ኛው ቀን 8፡30 ሰዓት ይከፈታል። 10ኛው ቀን በሥራ ቀን ላይ ካልዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን 8፡30 ሰዓት ይከፈታል።
- አንድ ተጫራች ባቀረበው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ 0939 500 000 / 0911 999 072
የገነት ሆቴል አስተዳደር