Addis Zemen (Aug 18, 2026)
የተሽከርካሪ ማሽነሪ ኪራይ እንዲሁም የከባድና የቀላል መኪና ጎማ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አኮኃ/ብግጨ/04/2018
የአባይ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት በአማራ ክልል በሚገኙ የተለያዩ የመስኖና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ ማሽነሪ፣ ቀላል እና ከባድ ተሽከርካሪዎች በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በኪራይ ማሰራት እንዲሁም የከባድ እና ቀላል መኪና ጎማዎችን ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ ድርጅቱ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን ይጋብዛል፡፡
1. የህጋዊነት ማስረጃዎችን ማለትም በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣ ለማሽነሪዎችና ከባድ ተሽከርካሪዎች ለመወዳደር የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርትፍኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡ ነገር ግን ለቀላል ተሽከርካሪዎች የቫት ተመዝጋቢ ካልሆኑ በስማቸው ደረጃ ለ ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፤ የሚያከራዩት ማሽነሪ/ተሽከርካሪዎች የባለቤትነት ማረጋገጫ (ሊብሬ) ኮፒውን በማያያዝ እና ለማመሳከሪያነት ኦሪጅናል ሊብሬ በውል ወቅት ማሳየት አለባቸው
2. የጨረታውን ዝርዝር ሁኔታ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
3. የሚያስፈልጉ የተሽከርካሪዎችና የማሽነሪዎች ብዛት በየቀጠናው (ከባቢያዊ ምድብ) እንደ ፕሮጀክቶች ቁጥር እየታየ የሚወሰን ሆኖ አይነታቸው እንደሚከተለው ይሆናል፡
|
ተ.ቁ |
የተሸከርካሪ /ማሽነሪ/ አይነት |
የስሪት ዘመን (እ.ኤ.አ) |
የክፍያ ሁኔታ |
የሚሰሩበት ቦታ /ፕሮጄክት |
|||
|
|
ሎት1 (የከባድና ቀላል ተሽከርካሪ እንዲሁም ማሽነሪ ኪራይ) |
||||||
|
1 |
ሲንግል ጋቢና (HZ) |
2000 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
2 |
ስቴሽን ዋገን– ላንድ ክሮዘር |
1998 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
3 |
ገልባጭ መኪና 6 ሜ/ኩ /150 ኩንታል እና በላይ |
2010 እና በላይ |
በቀን/በሜ3 |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
4 |
አይሱዚ ደረቅ ጭነት |
2000 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
5 |
ኤክስካቫተር በአካፋ በጃክሃመር |
ከ2010 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
6 |
ዶዘር |
ከ2008 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
7 |
ሎደር |
ከ2012 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
8 |
ግሬደር |
ከ2010 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
9 |
ስሙዝ ኮምፓክተር |
ከ2008 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
10 |
ሽፕ ፉት ኮምፓክተር |
ከ2008 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
11 |
ሻወር ትራክ |
ከ2000 እና በላይ |
በወር |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
12 |
ፊውል ትራክ |
ከ2000 እና በላይ |
በወር |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
13 |
ሎቤድ ትራክ |
ከ2005 እና በላይ |
በትሪፕ |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
|||
|
|
ሎት 2(የተሽከርካሪ ጎማ) |
||||||
|
|
የእቃው አይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
የማቅረቢያ ቦታ |
|||
|
14 |
የከባድና ቀላል ተሽከርካሪ ጎማ |
ቁጥር |
214 |
ባህርዳር ዋና መ/ቤት |
|||
4. ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች በኪራይ የሚገቡት ለመስኖ ፣መጠጥ ውሃ ግንባታ ፕሮጀክቶች & ለሰርቪስ እና ለሱፐርቪዥን አገልግሎት ነው፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ባህር ዳር ቀበሌ 16 ህዳሴ ሰፈር አመልድ ጋራጅ አባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ቢሮ ከግዥና አቅርቦት የሥራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 19 ማግኘት ይቻላል፡፡ እንዲሁም በኩባንያዉ ዌቭሳይት ማግኘት ይችላላ፡፡
6. ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው የተለያዩ ተሽከርካሪዎች/ማሽነሪዎች እና የተሽከርካሪ ጎማዎች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) በባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) በጨረታ ሰነዱ የተቀመጠውን የገንዘብ መጠን በአባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ስም ማስያዝ አለባቸው፡፡
7. ተጫራቾች በጨረታ ስነዱ ላይ በተገለፀው መሰረት የጨረታውን ሰነድ በታሸገ ፖስታ ለማሽነሪና ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ጨረታ እንዲሁም የተሽከርካሪ ጎማ ተብሎ ትክክለኛ ስምና አድራሻ በመፃፍ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ 15ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት በስራ ሰዓት ባህር ዳር ቀበሌ 16 ህዳሴ ሰፈር አመልድ ጋራጅ በሚገኘው የአባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ዋና መ/ቤት ግዥና አቅርቦት ስራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 19 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡
8. ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ
- በ15ኛው ተከታታይ ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ይዘጋል፤
- በ15ኛው ተከታታይ ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና አቅርቦት ስራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 19 ይከፈታል።
9. 15ኛው ቀን የበዓል ቀን ወይም እሁድና ቅዳሜ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ 8፡30 ይከፈታል።
10.ተጫራቾች በጨረታው ደንብና መመሪያ መሠረት ጨረታቸውን ማቅረብ አለባቸው፡፡ ከጨረታው ደንብና መመሪያ ውጭ የሚቀርብ ማንኛውም ጨረታ ተቀባይነት የለውም።
11.ተጫራቾች የሚያከራዩትን የማሽንና ተሽከርካሪ አይነት ብዛቱን ጭምር በዋጋ መሙያ ፎርሙ ላይ በግልጽ ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
12. አሸናፊው ድርጅት በጨረታ በተወዳደረበት ተሽከርካሪ እና ማሽነሪ ቁጥር ልክ መሣሪያዎችን ማቅረብ ይችላል።
13.አንድ ተወዳዳሪ ከራሱ መሣሪያና ተሽከርካሪ ውጭ የሚያቀርብ ከሆነ ከፍትህ ጽ/ቤት ሕጋዊ ውክልና እና የባለቤትነት ማስረጃ ሊብሬ ማያያዝ አለበት፡፡
14.ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊልም የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
15.ውድድሩ በነጠላ ዋጋ ነው፡፡
16. በጨረታው ለመሳተፍ ለሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከግዥና አቅርቦት ስራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 19 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም https://www.abayconstruction.org.et/auction-bid/ በስልክ ቁጥር 0912993321/0991021430 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
አባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር