የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን /አሚኮ/ የመዋቢያ ክፍልና ዳይሬክተር ኦፊስ ኢንተሬር ሥራ ደረጃ 8 የህንጻ ማስዋብ ሥራ ፈቃድ ያላቸዉ እና እስቲዲዮ ቢ የኢፖክሲ ሥራ ደረጃ 8 የህንጻ ማስዋብ ስራ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸዉን በግልጽ ጨረታ ተጯራቾችን አወዳድሮ አሸናፊዉን በመለየት ማሰራትና መግዛት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን /አሚኮ/ የመዋቢያ ክፍልና ዳይሬክተር ኦፊስ ኢንተሬር ሥራ ደረጃ 8 የህንጻ ማስዋብ ሥራ ፈቃድ ያላቸዉ እና እስቲዲዮ ቢ የኢፖክሲ ሥራ ደረጃ 8 የህንጻ ማስዋብ ስራ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸዉን በግልጽ ጨረታ ተጯራቾችን አወዳድሮ አሸናፊዉን በመለየት ማሰራትና መግዛት ይፈልጋል


Be'kur (Aug 20, 2026)

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 01/2019

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን /አሚኮ/

  • ሎት 1. የመዋቢያ ክፍልና ዳይሬክተር ኦፊስ ኢንተሬር ሥራ ደረጃ 8 የህንጻ ማስዋብ ሥራ ፈቃድ ያላቸዉ
  • ሎት 2. እስቲዲዮ ቢ የኢፖክሲ ሥራ ደረጃ 8 የህንጻ ማስዋብ ስራ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸዉን በግልጽ ጨረታ ተጯራቾችን አወዳድሮ አሸናፊዉን በመለየት ማሰራትና መግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ በጨረታዉ ለመወዳደር የሚፈለጉ ድርጅቶች፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ ለግንባታ ሥራዎች የከተማ ልማት የብቃት ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ሰርተፊኬት፣ ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ፎቶ ኮፒ አድርገው ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  2.  ተጫራቾች የሚጫረቱበት ጠቅላላ ድምር ዋጋ ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና ከዚያ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ ሰርተፊኬት ማያያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  3. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሎት 1. እና ሎት 2. በተከታታይ 21 /ሃያ አንድ ቀናት/ ከቀኑ 11፡30 ድረስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመግዛት አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ቢሮ ቁጥር 106 መግዛት ይችላሉ፡፡ የፋይናስ ሰነዶችን በመሙላት ኦርጅናል እና ኮፒ በማድረግ በጥንቃቄ በፖስታ በማሸግ የድርጅቱን ህጋዊ ማህተም፣ ፊርማና አድራሻ በትክክል በመሙላት ለዚህ ሲባል በተዘጋጀዉ የጨረታ ሣጥን ሎት 1. ሎት 2. በ22ኛዉ ቀን 4፡00 ድረስ ማስገባት አለባቸዉ፡፡
  4. ጨረታው ለሎት 1. እና ሎት 2. በ22ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይዘጋና በእለቱ ከረፋዱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ግዥና ንብረት ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክተር 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 104 ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ባይገኙም ጨረታው በእለቱ ይከፈታል፡፡
  5. የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ የተመሰከረለት ቼክ (ስፒኦ) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም ሲባል በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በቢሮው ገንዘብ ያዥ በኩል ደረሰኝ በማስቆረጥ የደረሰኙን ፎቶ ኮፒ ከጨረታው የፋይናንስ ሰነድ ፖስታ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ጨረታው የሚከፈትበት ሎት 1. እና ሎት 2. በ22ኛዉ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይዘጋና ከረፋዱ 4፡30 ይከፈታል፡፡ ቀኑ በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይዘጋና ከረፋዱ 4፡30 ይከፈታል፡፡
  7.  ቢሮው ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. የሚፈለጉትን የማዋቢያ ክፍልና ዳይሬክተር ኦፊስ ኢንተሬር ሥራ እና እስቲዲዮ ቢ የኢፖክሲ ሥራ ዓይነት፣ ብዛትና ስፔስፊኬሽን እንዲሁም የውል ቃሎች ከሰነዱ ጋር ተዘጋጅቶ የቀረበ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
  9.  የጨረታ ሰነዱን አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ቀበሌ 13 አየር መንገድ ከሚወስደዉ አስፓልት ገጠር መንገድ ከፍ ብሎ ባለዉ ህንጻ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 106 ድረስ በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
  10.  ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 320 97 35 ደውሎ መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን
ባሕር ዳር


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *