Addis Zemen (Aug 21, 2026)
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር WVD32/2017-oc
1) ኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር ለምርት ሥራ አገልግሎት የሚውል ሞዲፋይ ስታርች (Modify Starch) በሀገር ውስጥ ግለጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
2) በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ድርጅት የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል ከአክሲዮን ማህበሩ ቅ/ጽ/ቤት አዲስ አበባ ወይንም ከዋናው መሥሪያ ቤት ኮምቦልቻ መግዛት ይቻላል።
3) ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በትክክል በመሙላት በሰም በታሸገ ፖስታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በጨረታ መመሪያው ላይ የተገለጸውን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ በ(CPO) ወይንም በባንክ ጋራንቲ በማስያዝ ኮምቦልቻ ዋናው መ/ቤት ወይም አዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት ፓፓሲኖስ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 143 ወይም 144 እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ማቅረብ ይችላሉ።
4) ጨረታው ማስታወቂያው በተዘጋ በ3ኛው ቀን ኮምቦልቻ (ወሎ) በዋናው መሥሪያ ቤት ከጠዋቱ 4 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
5) ይህ ቀን የሕዝብ በዓል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይከፈታል።
6) አ/ማህበሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን መሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡–
ስልክ ቁጥር፡– 033-551 0627/ 551 0211/ 09 73 42 42 42 (ኮምቦልቻ)
ስልክ ቁጥር፡- 011-553 0124/ 551 3797/ 09 70 23 05 71 (አዲስ አበባ) ራስ ደስታ ዳምጠው ጎዳና ፓፓሲኖስ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ
የኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ አክሲዮን ማህበር