Addis Zemen (Sep 01, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
በሸገር ከተማ አስተዳደር ገላን ክ/ከ የሲዳ አዋሽ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2019 የበጀት ዓመት ለሰክቴር መ/ቤቶች አገልግሎት የምውሉ የተለያዩ:-
- የጽሕፈት መሳሪያ እና
- የጽዳት ዕቃዎች
- ፈርኒቸር
- ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች (ቋሚ ዕቃዎች)
- የደንብ ልብሶች አወዳድሮ ለማግዛት
ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተገለጸውን መመሪያ/መረጃ በማቅረብ/ ተጫራቾች በጨረታው እንድሳተፉ ይጋብዛል::
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የዋጋ ማቅረቢያ ዝርዝር (ሰነድ) ዋና እና ኮፒ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ /ፖስታ/ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15(አስራ አምስት) ተከታተይ የሥራ ቀናት ድረስ በሲዳ አዋሽ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ::
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምስክር ወረቀት ያላቸው እና የዘመኑ ግብር የከፈሉ እና ማስረጃ የሚያቀርቡ።
- በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ያላቸው ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15(አስራ አምስት) ተከታታይ የሥራ ቀናት ለአንዱ ሰነድ የማይመለስ ብር 1000 (አንድ ሺህ ብር) በሲዳ አዋሽ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ጽ/ቤት በመክፈል ሰነዱን ከሲዳ አዋሽ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ::
- በ16ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ(ተዘግቶ) ልክ በዚሁ ቀን ከረፋዱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሲዳ አዋሽ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ይከፈታል::ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል:: ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወክሎቻቸው የማይገኙ ከሆነ ጨረታውን ከመክፈት አይግደውም::
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 30,000 (ሰላሳ ሺህ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ/CPO/ ብቻ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል::
- ተጫራቾች የጨረታ አሸናፊነታቸው ከተገለፀላቸው በኋላ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይጠበቅባቸዋል::
- ተጫራቾች የጨረታ አሸናፊነታቸው ከተገለፀላቸው በኋላ በተገለፀላቸው ቀን ቀርቦው ውል ካልፈፀሙና የውል ማስከበሪያ ካላስያዙ የጨረታ ማስከበሪያው ለመንግስት ገቢ ይሆናል::
- ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ሰነድ ውስጥ በተገለፀው መሰረት የተመረተበትን ዕቃ ናሙና/sample/ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርበታል::
- ጥራት /Quality/ በሌላቸው እቃዎች ላይ (በኢትዮጵያ ደረጃ መዳቢዎች ከተሰጠ መስፈርት(standard) በታች የሚያቀርብ ተጫራች) መስሪያ ቤቱ የማይደራደር መሆኑን በቅድሚያ እናሳውቃለን::
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታው ሰነድ ላይ የተገለጹትንማንኛውንም ሁኔታዎች መለወጥ ወይም ማሻሻል ወይም ጨረታው ትቻለሁ ማለት አይችልም::
- ጽ/ቤታችን የሚያጫረታቸውን ዕቃዎች ብዛት እንደ አስፈላጊነታቸው እስከ (20%)በመጨመር ወይም በመቀነስ ማዘዝ ይችላል::
- የመወዳደሪያ በጨረታ ሰነዱ በተዘረዘረው መሠረት ተሞልቶ መቅረብ ይኖርበታል::
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0935205127/0941340508/0912047566 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ::
የመንግስት ፋይናንስ ህግ እና መመሪያን የሚጥስ ማንኛውም ነገር ተቀባይነት የለውም::
አድራሻ፡- በሸገር ከተማ ገላን ክ/ከ ሲዳ አዋሽ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
በሸገር ከተማ ገላን ክ/ከ የሲዳ አዋሽ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት