የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ለመ/ቤቱ ለሥራ አገልግሎት የሚውል እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ለመ/ቤቱ ለሥራ አገልግሎት የሚውል እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen (Sep 01, 2026)

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልጽ

የጨረታ ማስታወቂያ 02/2019

የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ለመ/ቤቱ ለሥራ አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተገለጸውን እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

  • ሎት1 . የክው ማኔጅመንት ሲስተም ዕቃዎችና አገልግሎትና ዝርጋታ ግዥ

በዚሁ መሠረት:

  1. በየዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያለው ፤ የዘመኑን ግብር የገበረ
  2.  የቫት VAT ተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ያለው
  3. የግብር ከፋይ /TIN መለያ ቁጥር ያለው
  4. የዕቃና የአገልግሎት አቅራቢነት ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ ድርጅቶች
  5. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሰውን ማስረጃዎች ኦርጅናልና ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታውን ሠነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ለእያንዳንዱ ሎት ሰነድ የማይመለስ ብር 200 ( ሁለት መቶ ብር) ብቻ በሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000347602028 በማስገባት እስልፒ ይዞ ሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቢሮ ቁጥር 230 በመቅረብ ሠነዱን መውሰድ ይቻላል።
  7.  ተጫራቾች ለሚያቀርቡት የጨረታ ዋጋ ማስከበሪያ በCPO / በ Bid Bond የ90 ቀን/ ብር 15,000/አስራ አምስት ሺህ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስም በማሰራት ማቅረብ የሚችል፡፡
  8. ተጫራቾች የፋይናሻል ዶክመንት ኦርጂናል 1 እና 2 ኮፒ በተለያየ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ለጨረታ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ መክተት ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጂናል 1 እና ኮፒ፣ በተለያየ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት አየር ላይ የሚውል ሲሆን በ11ኛው ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተዘግቶ 8፡45 ሰዓት ላይ ተጫራቾች | ህጋዊ ወከሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ዕለቱ በዓል / የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተገለጸው ሰዓት ይከፈታል፡፡
  10. የጨረታ አሸናፊ ዕቃውን በራሱ ወጪ አጓጉዞ መጋዝን ማስገባትና ሰነዱ ላይ በተገለጸው መሰረት አገልግሎቱን ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  11. የጨረታው አሸናፊ በጨረታ መመሪያ መሠረት የጨረታ አሸናፊነቱ በማስታወቂያ ይገለጻል።
  12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0462125584

የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *