Be'kur (Aug 31, 2026)
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የላይ አርማጭሆ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለወረዳው የመንግስት መኪኖች አገልግሎት የሚውል የመኪና መለዋወጫ አመታዊ ኮንትራት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው።
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው።
2. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ።
3. ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት እስከ 15ኛው ቀን ድረስ ሰነዱን በመግዛት በላይ አርማጭሆ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባችሁ።
4. ጨረታው በጋዜጣ በወጣ በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ በዚያው ቀን በ4፡30 በግልጽ ይከፈታል።
5. ዝርዝር መረጃን ከጨረታ ሰነዱ ጋር ከሚገኘው ማስታወቂያ ታገኛላችሁ።
ማሳሰቢያ፡- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የላይ አርማጭሆ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት