Addis Zemen (Sep 02, 2026)
የጨረታ ማስታሠዊያ
የጨረታ ቁጥር ኢ.ግ.ስ.ኮ/ብግጨ/5/2018
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከጨረታ ሰነዱ ጋር በተያያዘው መስፈርት መሠረት ተጫራቾችን አወዳድሮ በአዲስ አበባ ከተማ የኮርፖሬሽን ይዞታ በሆነውና በነጋ ቦንገር ህንፃ አካባቢ የሚገኙ ሱቆችን ለማከራየት ይፈልጋል፡፡
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅቶች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ፣ የዘመኑን ግብር ለመክፈላችሁ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣ የቫት ተመዝጋቢና የግብር ከፋይ የምዝገባ ሠርተፊኬት (TIN) እንዲሁም ከገቢዎች ጽ/ቤት ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ሰዓት አዲስ አበባ በሚገኘው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ፋይናንስ ዘርፍ ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቀርበው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ::
ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ማስከበሪያ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በሲ.ፒ.ኦ ወይም በባንክ ጋራንቲ (Unconditional) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል::
ጨረታው መስከረም 5/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ መስከረም 5/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የጨረታ ሰነድ የመክፈቻ ስነ–ሥርዓት ይከናወናል፡፡ ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ፦ ስልክ 0949632090/0911912222
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን