የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ የደረሰኞች ህትመት አገልግሎት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ የደረሰኞች ህትመት አገልግሎት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል


Reporter (Sep 13, 2026)

የጨረታ ማስታወቂያ

የሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ ቁጥር 10/2019

  1. የደረሰኞች ህትመት አገልግሎት ግዥ

በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የሚከተሉትን ህጋዊ ሰነዶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፦

    • የታደሰ ንግድ ፍቃድ
    • ቫት ተመዝጋቢ
    • ታክስ ክሊራንስ
    • በግዥ ባለስልጣን የምዝገባ ማስረጃ
    • የታክስ ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት
    • በዘርፉ የአቅራቢነት ምዝገባ ሠርተፍኬት ወረቀት
  • ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ለ 30 (ሰላሳ) ቀናት
  • የጨረታ ማስከበሪያ መጠን የደረሰኞች ህትመት አገልግሎት ግዥ 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ሆኖ የጨረታ ማስከበሪያው በሲ.ፒ.ኦ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና መሆን ይኖርበታል::
  • ሰነድ ለመግዛት የምትፈልጉ ተጫራቾች ሰነዱ በሚገኝበት በኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ዋና መስሪያ ቤት በፋይናንስ ክፍል ቢሮ ቁጥር 01 የማይመለስ 300.00 (ሶስት መቶ) ብር በመክፈል
  • የጨረታ ሰነድ ሶፍት ኮፒውን በግዥ ክፍል መውሰድ ትችላላችሁ::
  • የጨረታ ማስረከቢያ የመጨረሻ በቀን፣ወር እና ሰዓት 15/01/2019 ዓ.ም እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ይሆናል::
  • ጨረታው የሚከፈተው፡- በዕለቱ በቀን፣ወር እና ሰዓት 15/01/2019 ዓ.ም ከቀኑ 9፡30 ሰዓት ይሆናል:: 
  • ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
  • ለበለጠ መረጃ እና ማብራሪያ ዋናው መስሪያ ቤት በአካል በመገኘት ወይም በስልክ 0114171703 ወይም 0973480047 መጠየቅ ይቻላል::

አድራሻ፡- የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ (ዋና መስሪያ ቤት ቱሉ ዲምቱ)


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *