Addis Zemen (Sep 15, 2026)
የግልጽ ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01 2019 ዓ.ም
የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
የደቡብ ምዕ/ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል እቃዎችን የ2019 በጀት ዓመት የአንደኛ ዙር ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን፡
- ቋሚና አላቂ እቃዎች፣
- የደንብ ልብስና ጫማ፣
- መጋረጃ፣
- የፅዳት እቃዎች
- የመኪና ዕቃና ጎማ
ከሀገር ውስጥ ተጫራቾች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ስለሚፈልግ በጨረታው ለመሳታፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መመሪያዎች አሟልተው መገኛት ይኖርባቸዋል።
- በንግድ ዘርፍ ወይም በመስኩ በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ መረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- የመንግስት ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት ወቅታዊ የሆነ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም ቫት ከፋይነት የምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው።
- የአቅራቢዎች ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው።
- ግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (ቲን) ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- ከላይ በተራ ቁጥር 1 ላይ የተገለጹ የንግድ ፈቃድ ፎቶ ኮፒ የኦርጅናሉን ይዘት በጠበቀ መልኩ በግልጽ የሚነበብ መሆን አለበት።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000 (አምስት ሺህ) ብር ሕጋዊ ከሆነ ባንክ የተረገጋጠ (CPO) በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ስም አሰርተው ከሚያቀርባቸው ሠነዶች ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው። ይህ አንዳላ ሆኖ የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ አስቀድሞ ከባንክ ማረጋገጫ የሚወሰድ ይሆናል።
- ማንኛውም ተጫራች በተራ ቁጥር 7 ላይ የተጠቀሰውን (CPO) ካላቀረበ ከውድድር ውጪ ይሆናል።
- ለጥቃቅን ኢንተርፕረይዞች ለጨረታ ማስከበሪያ (CPO) ፋንታ ከአደራጁ መ/ቤት የተጻፈ ወቅታዊ የሆነ ሕጋዊ የድጋፊ ደብዳቤ መቅረብ ይኖርበታል።
- ተጫራቾች ለጨረታው የተዘጋጀውን ዶክመንት ወይም የጨረታው ሰነድ ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድቤት ወሊሶ ከተማ ቢሮ ቁጥር 12 ድረስ በአካል በመቅረብ የዕቃውን ምድብ አይነት /lot/ የማይመለስ 100/አንድ መቶ ብር/ ይህ ማስታወቂያ በዚህ ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ05/01/2019 እስከ 25/01/2019 ዓ.ም መግዛት ይችላሉ።
- ጨረታውን ለማሰናከል የሚሞከር ተጫራች ከጨረታው ውጪ ሆኖ ወደፊት በሚደረገው በማንኛውም ጨረታ ላይ እንዳይሳተፍ ይደረጋል፤ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብም ለመንግስት ገቢ ይሆናል።
- የጨረታው ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15ተከታታይ የስራ ቀናት ብቻ የሚቆይ ይሆናል።
- የጨረታው ሰነድ በ 26/01/2019 ከጠዋቱ እስከ 4:00 ድረስ ለጨረታ በተዘጋጀለት የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው የሚከፈተው በዚህ እለት 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል።
- መስሪያ ቤቱ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆና በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ከላይ በተራ ቁጥር 1-14 ሳያሟላ የሚቀረብ ተጫራች ከጨረታው ውጪ ይሆናል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
አድራሻ፡-የደቡብ ምዕ/ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ወሊሶ ከተማ
ስልክ ቁጥር፡- 0113411484/0113411396
Email: mmosk@oromiyaa.gov.et ማብራሪያ መጠየቅ ይችላሉ
የደቡብ ምዕ/ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት