Reporter (Aug 19, 2026)
የቢራ ሠራተኞች አጠቃላይ ንግድ ሥራ አክሲዮን ማህበር
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር ቢራሮ 01/2018-12
1. የንብረቱ ዝርዝር መግለጫና አድራሻ
ሀ, አድራሻ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ቦርከና ክፍለ ከተማ።
ለ, ልዩ ቦታው ኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ አክሲዮን ማህበር ጎን።
ሐ, የመሬት ስፋት 12,122.06 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ መዋለ ህፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት።
መ, የይዞታው የአሁኑ አገልግሎት ለንግድ ሥራ አገልግሎት የሚውል ይዞታ ነው።
ሠ, ጨረታው የሚቆይበት ጊዜ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 20 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ሲሆን ኮምቦልቻ ዋናው መስሪያ ቤት እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ ይችላሉ።
2. ለተጫራቶች የሚቀርቡ ሕጋዊ መስፈርቶች
ሀ, ተጫራቶች የታደሰ ንግድ ፈቃድ ወይም ብሔራዊ መታወቂያ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
ለ, በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00(አምስት መቶ) ብቻ ከዋናው መስሪያ ቤት ኮምቦልቻ (ወሎ) መግዛት አለበት::
ሐ, የጨረታ ማስከበሪያ (የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1689) ተጫራቶች የወሰዱትን ግደታ ለማረጋገጥ የሚሆንና በታወቀ ባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (CPO) ከጠቅላላ ካቀረቡት ዋጋ 1% ዋስትና ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ አለባቸው።
መ, ጨረታው ማስታወቂያው በተዘጋ በ3ኛው ቀን ኮምቦልቻ (ወሎ) በዋናው መስሪያ ቤት ከጧቱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቶች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡ ሆኖም ይህ ቀን የህዝብ በዓል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይከፈታል።
3. የአክሲዮን ማህበሩ መብት
ሀ, አክሲዮን ማህበሩ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉበሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብት በህግ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
ስልክ ቁጥር 0912 395 167 / 0970 638 884
(ኮምቦልቻ)