በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሰዲል ለኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የተለያዩ እቃዎችን ግዥ መፈጸም ይፈልጋል – test3.diretenders.com

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሰዲል ለኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የተለያዩ እቃዎችን ግዥ መፈጸም ይፈልጋል


Addis Zemen (Sep 12, 2026)

ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የግዥው መለያ ቁጥር 001/2019

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሰዲል ለኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አስተዳደር ጽህፈት ቤት ስር ላሉት ጽህፈት ቤቶች በ2019 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን፡-

  • ሎት 1 6211 የደንብልብስ- 15,002ብር 
  • ሎት 2 6212 አላቂ የቢሮ እቃዎች-  10,770 ብር
  • ሎት 3 6213 ህትመት- 1,610ብር
  • ሎት 4 6215 የትምህርት አላቂ እቃዎች- 15,624 ብር
  • ሎት 5 6218 የፅዳት እቃዎች- 8,600ብር
  • ሎት 6 6219 የተለያዩ መሳሪያዎች መፅሃፍት- 4,140ብር
  • ሎት7 6313 ቋሚ የቢሮ የማሽነሪ እቃዎች- 17,967 ብር
  • ሎት 8 6244 የተለያዩ ጥገናዎች- 4,300 ብር
  • ሎት 9 6255 የጭነት -4550 ብር
  • ሎት10 6232 የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ–1,550 ብር

ብቃት ያላቸውንና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል

በዚህም መሰረት

በጨረታው ለመወዳር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በመንግስት ግ/ን/አስ/ኤጀንሲ ድህረ ገጽ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገቡ፣ የቲን እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ

1. ት/ቤቱ የሚጫረተውን እቃ ብዛት እንደአስፈላጊነቱ በመጨመር ወይም በመቀነስ ማዘዝ የሚችል ሲሆን ተጫራቾች ላሸነፉት እቃ የ6 /ስድስት/ ወር ዋስትና መስጠት አለባቸው።

2. በጨረታው ያሸነፉ ተጫራቾች የዕቃውን 10% (ሲፒኦ) ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል።

3. ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት አንስቶ በተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 150.00 (አንድ መቶ ሃምሳ) በመክፈል በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሰዲል ለኢትዮጵያ 2ኛ ደ/ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 004 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።

4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት በት/ቤቱ የመ/ፋ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 004 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ10 አስረኛው ቀን በ11 ሰአት ታሽጎ በማግስቱ ከቀኑ 4፡00 ሰአት በት/ትቤቱ ቅጥር ገቢውስጥ ቢሮ B1-002 ቁጥር ይከፈታል፡፡ የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበአል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰአት ታሽጎ ይከፈታል።

6. ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ሎት1፣ ሎት2፣ሎት3፣ ሎት4፣ሎት5፣ሎት 6 እና ሎት7እና ሎት8፤ሎት9፤ሎት10 ናሙና ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን በየሎት ከሎት 1 እስከ ሎት 10 በቀረበው የፍላጎት መግለጫ መሰረት የተሟላ የፍላጎት መግለጫ ማዘጋጀትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

7. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።

8. የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም።

9. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈጻሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

10. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

በተጨማሪ ለማብራሪያ ጥያቄ አድራሻ፡- በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ከወረዳ 05 አስ/ፅ/ቤት ወይም ከቀድሞ ቀበሌ 42 ቄራ አልማዝዬ ሜዳ አለፍ እንዳሉ ያገኙታል

የመ/ቤቱ ስልክ ቁጥር፡-011467-43-67/68/69
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሰዲል ለኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት