Addis Zemen (Sep 17, 2026)
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ምዕ/ኢ/ህ/ክ/መ/ የአንድራቻ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ሰ/ጽ/ቤት በወረዳ ውስጥ ለሚገኙት ሴክተር መ/ቤቶች ሥራ አገልግሎት የሚውል ኤሌክትሮንክስ መሳሪያዎች፤ ፈርኒቸር፣ ጄኔሬተር ሞተርሳይክል፤ የጽህፈት መሳሪያና የጽዳት ዕቃዎችና የእንስሳት መድሀኒት በዘርፉ የተሰማሩትን ህጋዊ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት ተጫራቾች ለጨረታ ብቁ የሚያድርጓቸው፤
- አግባብነት ያለው የታድሰ ንግድ ስራ ፈቃድ፤የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፤የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉና ፈቃዳቸውን ያሳደሱ ተጫራቾችን ይጋብዛል።
- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500/አምስት መቶ/ በአን/ወ/ገ/ቅ/ጽ/ቤት በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከአን/ወ/ፋይ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ግዥ/ንብ/አስ/ር ስራ ሂደት ቢሮ ቁ 11 መረከብ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድና ዋጋ የተሞላበት ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ሰነድ ኦሪጅናልና እያንዳዱን ሁለት ኮፒ በፖስታ በማሸግ ማቅረብ የሚችል/ትችል።
- ተጫራቾች 10000/አስር ሺህ/ብር የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ/ CPO/ ማቅረብ የሚችል/ትችል።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበትቀን ጀምሮ ለ21 የስራ ቀናት አየር ላይ ይቆያል።
- ጨረታው በ22ኛ ሥራ ቀን በጧቱ 3.00/ሶስት /ሰዓት ላይ ታሽጎ በዕለቱ ከበጧቱ 4፡30/ አራት ሰዓት ተኩል/ ላይ ተጫራቾች ሠይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ካልሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ይከፈታል።
ማሳሰቢያ
- መ/ቤቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨርታውን ሙሉበሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
- በጨረታ ከፈታ ወቅት ተጫራቾች ወይንም የወኪሎቻቸው ያለመገኘት ጨረታውን አያስተጓጉልም ፤
- ለበለጠ ማብራሪያ አን/ወ/ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት ግዥንብ/አስ/ር ሥራ ሂደት መጠየቅ ይቻላል።
በደ/ምዕ/ኢ/ህ/ክ/መ/ የአንድራቻ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ጽ/ቤት