Your cart is currently empty!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምገባ ኤጀንሲ ለ2018 በጀት አመት የሚገለገልባቸውን የተለያዩ አይነት የአገልግሎቶች እና የእቃ ግዥዎችን በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Sep 02, 2025)
የጨረታ ጥሪ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጨረታ መለያ ቁጥር፡– አ/አ/ከ/አስ/ምገባ ኤጀንሲ/ብ.ግ.ጨ/እ.ግ/01/2018 እና አ/አ/ከ/አስ/ምገባ ኤጀንሲ/ብ.ግ.ጨ/አገ.ግ/02/2018 ምገባ ኤጀንሲ ለ2018 በጀት አመት የሚገለገልባቸውን የተለያዩ አይነት የአገልግሎቶች እና የእቃ ግዥዎችን በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ ፈቃደኛ የሆናችሁ ተጫራቾች እንድትሳተፉ እየጋበዝን እቃዎቹ እና አገልግሎቶቹ እንደሚከተሉት ተዘርዝረዋል፡፡
ምድብ ቁጥር |
የሚገዛው እቃ/አገልግሎት/ አይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ ብር |
ሎት 1 |
የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ግዥ |
25,000 ብር |
ሎት 2 |
የፅዳት እቃዎች ግዥ |
7,000 ብር |
ሎት 3 |
የፅህፈት መሳሪያዎች ግዥ |
12,000 ብር |
ሎት 4 |
የኘሪንተር እና የፎቶ ኮፒ ቀለም ግዥ |
8,000 ብር |
ሎት 5 |
የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አበባ ግዥ |
5,000 ብር |
ሎት 6 |
የደንብ ልብስ እና ስፌት አገልግሎት ግዥ |
2,000 ብር |
ሎት 7 |
መጋረጃ እና የወለል ምንጣፍ ግዥ |
2,000 ብር |
ሎት 8 |
የመኪና እቃዎች እና አልባሳት ግዥ |
10,000 ብር |
ሎት 9 |
የትራንስፖርት አገልግሎት ግዥ |
20,000 ብር |
ሎት 10 |
የህትመት ስራ አገልግሎት ግዥ |
18,000 ብር |
ሎት 11 |
የመስተንግዶ አገልግሎት ግዥ |
15,000 ብር |
ሎት 12 |
የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ጥገና አገልግሎት ግዥ |
10,000 ብር |
ሎት 13 |
የአጥር ፣ የኤሌክትሪክ ጥገና እና የፓርቲሽን ስራ አገልግሎት ግዥ |
20,000 ብር |
ሎት 14 |
የፈርኒቸር እቃዎች እና ሌሎች የጥገና አገልግሎት ግዥ |
15,000 ብር |
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
1. በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3. ተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የያዘ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 300/ ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል የምትወስዱ መሆኑን እየገለፅን ይህ ጨረታ በአየር ላይ የሚቆየው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10/አስር/ ተከታታይ የስራ ቀናት ይሆናል፡፡
5. ጨረታው ሰነድ መመለሻ የመጨረሻ ቀን 07/01/2018 ዓ.ም 8፡30 ሰዓት ነው
6. ጨረታው በቀን 07/01/2018 ዓ.ም በ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በቀን 07/01/2018 ዓ.ም በ4፡00 ሰዓት ይከፈታል
7. ተጫራቾች ሌሎች መረጃዎችን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
8. ኤጄንሲው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
9. የጨረታ ሰነዱ ፒያሳ ኤሊያና ሆቴል ፊት ለፊት(ዶን የጥርስ ህክምና) ያለበት ህንጻ ላይ 8ኛ ፎቅ ግዥና ንብረት ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ይገኛል
አድራሻ፡– ፒያሳ ኤሊያና ህንጻ ፊት ለፊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቤተክህነት (ዶን የጥርስ ህክምና ያለበት) ህንጻ ላይ 8ኛ ፎቅ የግዥና ንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር +251-11-812 8321
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምገባ ኤጀንሲ