Your cart is currently empty!
ቡና ባንክ አ.ማ ተሽከርካሪ በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Reporter(Sep 07, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የሐራጅ ማስታወቂያ
ቁጥር፤ ቡባ/ሕአዳ/ሐራጅ/038/2017
ቡና ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ቀጥሎ የቀረበውን ንብረት በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::
ተሽከርካሪ
| ተ.ቁ | የተበዳሪ ስም | የንብረት አስያዥ ስም | አበዳሪ ቅርንጫፍ | የሰሌዳ ቁጥር | የመያዣ አይነት/ ሞዴል | የሻንሲ ቁጥር/ ሴሪያል ቁጥር | የሞተር ቁጥር | የጨረታ መነሻ ዋጋ በብር | የጨረታ ቀን እና ሰዓት | ጨረታው የወጣው | |
| ቀን | ሰዓት | ||||||||||
| 1 | አቶ አሰፋ ዘሪሁን አደመ | ተበዳሪ | ቦሌ 18 | ኢት-03-94080 | የ2017 ምርት ሲኖ ትራክ | LZZ5BLSF2 HA256679 | WD615.47* 170607031337* | 7,000,000.00 | መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም | 3፡00-4፡00 | ለሶስተኛ ጊዜ | 
| ኢት-03-94338 | የ2017 ምርት ሲኖ ትራክ | LZZ5BSF3 HN197814 | WD615.47* 161107041117* | 7,000,000.00 | መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም | 4:00-5:00 | ለሶስተኛ ጊዜ | ||||
የሐራጅ ደንቦች፣
1. ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4ኛ) በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በቡና ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ::
2. አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ አሸናፊ መሆኑ በደብዳቤ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ ባሉት በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ ተጠቃሎ መከፈል አለበት:: ካልተከፈለ የተያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል:: በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃሉ:: ላላሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ በዕለቱ ይመለስላቸዋል::
3. በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ብቻ ናቸው:: ተበዳሪ እና ወኪሎቻቸው ባይገኙም ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል::
4. የተጫራቾች ምዝገባ ከእያንዳንዱ የንብረት ሐራጅ መዝጊያ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል:: በሐራጁ የመጨረሻ ሰላሳ ደቂቃዎች የተጫራች ምዝገባ አይካሄድም::
5. የሐራጁ አሸናፊ /ገዢ/ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፤ ግብር በዋጋው ላይ የሚታሰብ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (15%) ካለ ከስም ማዛወሪያ ክፍያ ጋር የተገናኙና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ታክስ እና ግብሮች ገዥው /አሸናፊው/ ይከፍላል::
6. በሐራጁ የተዘረዘሩትን ንብረቶች ለማየት ከአበዳሪ ቅርንጫፉ ጋር በመነጋገር ፕሮግራም አስይዞ መጎብኘት ይቻላል::
7. ተጫራቹ የጨረታው አሸናፊ ነው የሚባለው አሸናፊነቱን የሚገልፅ ደብዳቤ በጽሑፍ ሲደርሰው ብቻ ነው::
8. ጨረታው በቡና ባንክ አ.ማ ዋናው መስሪያ ቤት ቦሌ ክፍለ ከተማ፤ ከወሎ ሰፈር አደባባይ ወደ ቦሌ ሲሄዱ ሩዋንዳ መታጠፊያ ሳይደርሱ በሚገኘው የባንኩ ሕንፃ 9ኛ ፎቅ በሚገኘው አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል::
9. ባንኩ የተሻለ አማረጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ ፣ ሕግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ስ.ቁ 011-1-58-08-63/011-1-26-36-09፣ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።