Your cart is currently empty!
የሆሣዕና ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚዎች ምግብ ለማብሰል አገልግሎት የሚውል የባህር ዛፍ የማገዶ እንጨት አቅርቦት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 21, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የማገዶ እንጨት አቅርቦት ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡– ሆማተ/822/2018
የሆሣዕና ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚዎች ምግብ ለማብሰል አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች በሠንጠረዡ ውስጥ የተመለከቱትን ባህር ዛፍ የማገዶ እንጨት አቅርቦት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በቅድሚያ ለአንድ ዓመት በሚቆይ የአቅርቦት ጊዜ ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በአቅራቢና ተቀባይ መካከል በሚደረገው የውል ስምምነት መሠረት እስከ ሶስት ዓመታት ለሚደርስ ጊዜያት ማለትም እስከ ጥቅምት 2021 ድረስ እየተራዘመ የሚሰራ የግዥ ሂደት እንዳለ ታሳቢ በማድረግ፤ በማዕቀፍ ስምምነት በየወሩ ለሚያቀርቡ አቅራቢዎች በጨረታ አወዳድሮ ለአሸናፊ ተጫራች ለመስጠት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡–
| ተ.ቁ | የአቅርቦቱ አይነት | መለኪያ | የአቅርቦት መጠን | የማቅረቢያ ጊዜ | ርክከቡ የሚፈፀሚበት ቦታ | ለአቅርቦቱ በማዕቀፍ ስምምነቱ መሠረት በቅድሚያ ለ01 ዓመት ቆይታ ጊዜ ከ…እስከ | 
| 1 | ባህር ዛፍ ግንድላ የማገዶ እንጨት | በሜ/ኩብ | ከ250-450 ሜ/ኩብ | ወር በገበ ከ25-30 | ማረሚያ ተቋም | ከ01/03/18 ዓ.ም-30/02/2019 ዓ.ም | 
መመዘኛዎች፡–
(01) በየመስኩ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው፤ ከማንኛውም ግብርና ታክስ ከፋይነት ነፃ እንዲሆኑ ከተፈቀደላቸው ድርጅቶችና ዩኒየኖችና ተመሳሳይ የንግድ ድርጅቶች በስተቀር የVAT 15% ተመዝጋቢ የሆኑና የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማስረጃ ሊያቀርቡ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
(02) ተጫራቾች ለሚጫራቱበት አቅርቦት በቀደምት የሥራ ዘመን ተጫርተው በማሸነፍ ለማረሚያ ተቋማት ወይንም ለሌሎች መንግስታዊና ሕዝባዊ ድርጅቶች ለ01 (አንድ) አመት እና ከዚያም በላይ ለሆነ ጊዜያት ያለእንከን ስለማቅረባቸው የመልካም ሥራ አፈፃፀም ደብዳቤ /ምስክር/ ወረቀት ማስረጃ ከሌሎች መጫረቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፤
(03) አሸናፊው ተጫራች ለአቅርቦቱ ከላይ በተዘረዘሩት መስፈርቶች መሠረት በቅድሚያ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ12 /አስራ ሁለት/ ወራቶች በየወሩ ለማቅረብ ህጋዊ የውል ሰነድ የሚፈርምና በቅድሚያ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሸናፊው ነጠለላዋጋ እንደተጠበቀ ሆኖ በየጊዜው የእንጨት ዋጋ ማስተካከያ በማዕከላዊ ስታቲክስ ኤጀንሲ ሊደረግና ሊሻሻል የማይችል ቢሆን እንኳ ባሸነፉት ዋጋ ለማቅረብ ፈቃደኛ የሆኑ፤
(04) ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሆሣዕና ማረሚያ ተቋም ግዥና ፋይናንስ ንብ/አስ/የሥራ ሂደት ቢሮ በአካል በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በነፃ መውሰድ የሚችሉ ሲሆን የጨረታ ማስከበሪያን በሚመለከት ለማገዶ እንጨት ከጠቅላላ አቅርቦት ዋጋ 10% የብር 30,000 /ሰላሳ ሺህ/ CPO/ተመሳሳይ/ ሰነድ በማሰራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
(05) ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አሥራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት የእያንዳንዱን የማገዶ እንጨት ነጠላ ዋጋ ከነማስረጃው ኮፒዎች ጋር በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ አዘጋጅተው ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
(07) ጨረታው በ15ኛው ቀን በ11፡30 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች /ህጋዊ/ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 16ኛው ቀን በ4፡30 ሰዓት በማረሚያ ተቋሙ ቅጥር ግቢ አዳራሽ/ ቢሮ የሚከፈት መሆኑን ስንገልጽ ዕለቱ የበዓላት/ የዕረፍት ቀን ከሆነ በማግስቱ በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እያሳሰብን መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-09-26-20-08-23/ 09-12-05-28-32 ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የሆሣዕና ማረሚያ ተቋም