Your cart is currently empty!
የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ለመጪው ፋሲካ ባዛር በመስቀል አደባባይ መዝናኛ ቦታ የብስክሌት አገልግሎት የሚሰጡ ቦታዎችን ማከራየት ይፈልጋል
Reporter(Feb 08, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ 018/2018
የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ለመጪው ፋሲካ ባዛር በመስቀል አደባባይ መዝናኛ ቦታ የብስክሌት አገልግሎት የሚሰጡ ቦታዎችን ማከራየት ይፈልጋል።
ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራና በጨረታዉ መሳተፍ የሚፈልግ ድርጅት ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን መስቀል አደባባይ በሚገኘው የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ማግኘት ይችላል።
1. ተጫራቾች የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምሰክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ እና PTIN ወይም TOT ሰርተፊኬት ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
2. ጨረታው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማለትም ከየካቲት 1 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ የካቲት 09 ቀን 2018 ዓ.ም ለ7 ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ8ኛው ቀን የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡15 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት የኤግዚቢሽን ማዕከልናየገበያ ልማት ድርጅት መ/ቤት ተጫራቾች እና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
3. በዘርፉ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ብር 500 አምስት መቶ ከፍለው መግዛት ይችላሉ።
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድቦንድ ለሚወዳደሩበት በባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ CPO} ብር 50,000.00 (ሀምሳ ሺህ ብር) ማስያዝ አለባቸው።
6. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸዉን እና የጨረታ ማስከበሪያዉን በተለያየ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ተጫራች ድርጅቶች ለሚያቀርቡት ዋጋ ለእያንዳንዱን የቦታ ካሬ ስፋት ነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ በትክክል ሞልተው በግልፅ ማስቀመጥ አለባቸው።
7. ይህ ጨረታ በድርጅቱ የግዥ መመሪያ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል።
8. የጨረታዉ አሸናፊ አሸናፊነቱ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ 3 ቀናት ዉስጥ የጠቅላላ ዋጋዉን ገየዉል ማስከበሪያ ያለቅድመ ሁኔታ ለገዥ የሚከፈል (Unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ዉል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል።
9. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በዚህ ጨረታ አይገደድም ወይም ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
10. ማሳሰቢያ፡ ውድድሩ የሚካሄደው መስቀል አደባባይ ባለው 500 ሜትር ካሬ በሚሸፍን ለብስክሌት የሆነ ቦታን መሠረት ያደረገ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 011-515 16 93 መጠየቅ ይችላሉ።
የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገቢያ ልማት ድርጅት