Your cart is currently empty!
የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርት ቢሮ በ2018ዓ.ም በጨረታ መለያ ቁጥር ግ.ጨ ባ/ቱ/ስ01/18 ለሚዛን አማን ስፖርት አካዳሚ የጅምናዚየም ስፖርት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ህጋዊ ፍቃድ ካላቸው ድርጅቶች እና ነጋዴዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Feb 11, 2026)
የስፖርት ጅምናዚየም ዕቃዎች ግዥ ማስታወቂያ
የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርት ቢሮ በ2018ዓ.ም በጨረታ መለያ ቁጥር ግ.ጨ ባ/ቱ/ስ01/18 ለሚዛን አማን ስፖርት አካዳሚ የጅምናዚየም ስፖርት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ህጋዊ ፍቃድ ካላቸው ድርጅቶች እና ነጋዴዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
የዕቃዎች ዝርዝር |
የጨረታ ማስከበሪያ ብር መጠን |
|
ምድብ -1 የጅምናዚየም ስፖርት ዕቃዎች |
ብር 50,000.00 |
በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፡–
1. በሚወዳደርበት ዘርፍ የዘመኑ ግብር የተከፈለበት ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ የምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የቫት ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ፣ የግብር ከፋይ መለያ TIN ሰርተፊኬት፣ እና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
2. ተጫራቾች በሚወዳደሩበት ጨረታ በንግድ ዘርፍ ያላቸውን ሰነዶች ኮፒውንና እንዲሁም ቢሮ ባዘጋጀው ኦርጅናል ጨረታ ሠነድ ላይ ዋጋ በመሙላት ኦርጅናሉንና ኮፒውን በፖስታ አሽጎ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
3. ተጫራቾች በጨረታው ለመካፈል የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በባንክ በተመሰከረ የባንክ ጋራንቲ ወይም CPO በተጠየቀው ገንዘብ መጠን ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራች ድርጅቶች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት በኢት/ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000454317754 ደ/ምዕ/ኢ/ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርት ቢሮ ስም የማይመለስ ብር 400.00 (አራት መቶ ብር) በመክፈል ኦርጅናል የባንክ ስልፕ ይዘው በመምጣት ከቢሮ ግ/ፋይ/ን/አስ/ር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ።
5. ጨረታው በ15ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግተው በዕለቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ደ/ምዕ/ኢ/ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርት ቢሮ ይከፈታል።
6. ሁሉም ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት CPO/ ባንክ ጋራንቲ/ የሚመለስላቸው አሸናፊ ድርጅቶች ውሉን ሲፈራረሙና የውል ማስከበሪያ 10% CPO ሲያሲይዙ ይሆናል።
7. አሸናፊ ተጫራች ዕቃውን እስከ ቦታው በማምጣት ገጥሞ የሚያስረክብ ይሆናል።
8. ቢሮ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 39 12 62 16 / 09 17 83 17 15 መጠየቅ ይቻላል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ