Your cart is currently empty!
ዳሽን ባንክ አ.ማ በባንኩ የሚገኙ ያገለገሉ ቋሚ እቃዎችን ባሉበት ሁኔታና ቦታ ለአንደኛ ግዜ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Reporter(Aug 31, 2025)
Fortune(Aug 31, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የጨረታ ማስታወቂያ
የተለያዩ ቋሚ እቃዎች በግልጽ ጨረታ ለመሸጥ ለአንደኛ ጊዜ የተዘጋጀ ሽያጭ DB/035/2017
ዳሽን ባንክ አ.ማ በባንኩ የሚገኙ ያገለገሉ ቋሚ እቃዎችን ባሉበት ሁኔታና ቦታ ለአንደኛ ግዜ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ።
1. ተጫራቾች ቄራ አካባቢ በሚገኘው የባንኩ ህንጻ 3ኛ ፎቅ የንብረት ክምችትና ስርጭት ክፍል በመምጣት የጨረታውን መረጃ፣ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ ብቻ ከፍለው መውሰድ ይችላሉ፣
2. ተጫራቾች ሰነድ ገዝተው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከቀኑ 8፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ለሽያጭ የቀረቡ ንብረቶችን በባንኩ መጋዘኖችና ቦታዎች በመሄድ መመልከት ይችላሉ፣
3. ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ለእያንዳንዱ ዓይነት ለሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 20 ፐርሰንት የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝና በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ በባንኩ የንብረት ክምችትና ስርጭት ክፍል ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. የጨረታው መምሚያ መስፈርት ዋና የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ሲፒኦ እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን አሟልቶ መገኘት ነው።
5 ከላይ በተራ ቁጥር 4 የተገለፀውን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ያላስያዘ እና በሠነዱ የተቀመጡ ለሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል።
6 የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከአዲስ አበባ ውጪ ከሆነ ከዳሽን ባንክ አማ ቅርንጫፎች ብቻ መሆን ይኖርበታል፣ ሆኖም በጨረታው አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ክፍያ በየሎ ገቢ ማድረጋቸውን ለማረጋገጥ ክፍያው በዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች በተዚጋጀ ሲፒኦ ብቻ መሆን ይኖርበታል
7 የጨረታ ሳጥኑ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ላሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን፤ በ15ኛው ቀን ማለትም በመስከረም 07 ቀን 2018 ዓም ከቀኑ በ6፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ8፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኘበት ባንኩ የንበረት ክምችትና ስርጭት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መክፈት አያስተጓጉልም
8. በጨረታው አሸናፊ ተጫራቾች የአሸናፊዎች ዝርዝርማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ከ3 /ሶስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 2 /ሁለት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ የውል ዋጋውን 10 በመቶ በማቅረብ ከባንኩ ጋር ውል መፈራረምና ያሸነፉበትን ዋጋ በሙሉ መክፈል ይኖርባቸዋል። ሆኖም ከላይ በተገለጸው መሰረት ውል ካልፈረሙ ወይም ሙሉክፍያውን በተጠቀሰው ግዜ ገደብ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ለባንኩ ገቢ ይደረጋል።
9. ተጫራቾች ያሸነፉበትን ንብረት በራሳቸው ወጪ በማጓጓዝ ውል በፈረሙ በ10 የሥራ ቀናት ዉስጥ በማንሳት ማጠናቀቃቸው ሲረጋገጥ ያስያዙት የውል ማስከበሪያ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
10 ባንኩ ባው ጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ኩተገኘ ከውድድር ውድቅ ይደረጋል።
11. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 011-465 5552 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፣
12. ባንኩ ጨረታውን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል የሚችል ሲሆን በማናቸውም ጊዜ ጨረታውን ለመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
ዳሽን ባንክ አ.ማ
አዲስ አበባ
ተ.ቁ |
የንብረቱ አይነት |
መለኪያ |
ጠቅላላ ብዛት |
1 |
HIGH BACK CHAIR |
በጥቅል |
በጥቅል |
2 |
COUNTER CHAIR |
በጥቅል |
በጥቅል |
3 |
UPS |
በቁጥር |
7 |
4 |
Adding Machine |
በቁጥር |
7 |
5 |
FILE CABINET |
በቁጥር |
16 |
6 |
GUEST CHAR 2 & 3 SEALER |
በጥቅል |
በጥቅል |
7 |
GUEST CHAIR |
በጥቅል |
በጥቅል |
8 |
LOW BACK CHAIR |
በጥቅል |
በጥቅል |
9 |
Managerial table |
በጥቅል |
በጥቅል |
10 |
Single pedestal table |
በጥቅል |
በጥቅል |
11 |
Computer stand table |
በጥቅል |
በጥቅል |
12 |
STORAGE CABINET |
በቁጥር |
8 |
13 |
NOTE COUNTING MACHINE FOR TELLER |
በቁጥር |
261 |
14 |
Note counting machine for cashier |
በቁጥር |
46 |
15 |
PHOTOCOPY Machine |
በቁጥር |
26 |
16 |
FAX MACHINE |
በቁጥር |
11 |
17 |
KYOCERA PHOTOCOPY |
በቁጥር |
12 |
18 |
Child bed |
በቁጥር |
14 |
19 |
Four group Generator |
በቁጥር |
2 |
20 |
Kama small generator |
በቁጥር |
5 |
21 |
Kama Big generator |
በቁጥር |
2 |
22 |
Pramac Generator |
በቁጥር |
2 |
23 |
SYSTEM UNIT |
በቁጥር |
25 |
24 |
PASSBOOK PRINTER |
በቁጥር |
39 |
25 |
Kyocera printer |
በቁጥር |
36 |
26 |
HP LASERJET PRINTER |
በቁጥር |
5 |
27 |
SCANNER MN |
በቁጥር |
15 |
28 |
MONITOR |
በቁጥር |
31 |