Your cart is currently empty!
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/ለ/የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ በመጋበዝ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 16, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/ለ/የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ፡–
- LOT 1-Workshop Materials NCB/OACFLTD/AMF/01/2018
- LOT 2-Electrical Materials – NCB/OACFLTD/AMF/02/2018
- LOT 3-Electrical and Mechanical tools-NCB/OACFLTD/AMF/03/2018
- LOT 4-Bearing-NCB/OACFLTD/AMF/04/2018
- LOT 5-Mechanical Seal and Oil Seal-NCB/OACFLTD/AMF/05/2018
- LOT 6-Sheet Metals and Angle Iron-NCB/OACFLTD/AMF/06/2018
- LOT 7-Steam Valves and pipe – NCB/OACFLTD/AMF/07/2018
ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ በመጋበዝ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው።
1. ተጫራቾች የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው እና የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
2. የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ብቻ በፋብሪካችን አካውንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000257808697 ወይም በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ 1000043405229 በመከፈል /ገቢ በማድረግ/ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ከ2፡00-6፡00 ሰዓት፤ ከሰዓት በኃላ 7፡00-10፡00 ሰዓት ድረስ ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወስደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ህንፃ ስድስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ወይም አሰላ – ቁሉምሳ ከሚገኘው ፋብሪካችን ቢሮ ቁጥር 003 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
3. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በፖስታ በማሸግ አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና መ/ቤት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ከተጠቀሰው የመዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራቾች ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለ LOT 1 ብር 15,000.00፣ ለLOT 2 ብር 15,000.00፣ ለLOT 3 ብር 10,000.00፣ ለLOT 4 ብር 10,000.00፣ ለLOT 5 ብር 5,000.00፣ ለLOT 6 ብር 10,000.00፤ ለLOT 7 ብር 10,000.00 በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ (CPO) ለየብቻ በማስያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በ22ኛው ቀን LOT 1 እና LOT 2 በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ሰዓት ላይ፤ LOፕ 3 እና LOT 4 በ5፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ5፡30 ሰዓት ላይ፤ LOT 5፣ LOT 6 እና LOT 7 ልክ በ5፡40 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ6፡10 ሰዓት ላይ ለመገኘት በሚሹ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና መ/ቤት የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃላ/የተ ሰባተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። የመክፈቻው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
6. ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
7. ተጫራቾች በጨረታ ማስታወቂያና በተጫራቾች መመሪያ ላይ ግልጽ ያልሆነ ነጥብ ካለና ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 09-65-65-04-81/ 09-65-65-02-85 በሥራ ሰዓት ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃላ/የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ