Your cart is currently empty!
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት ጎፋ ዞን ፋይናንስና ፕላን መምሪያ የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል
Addis Zemen(Feb 04, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የጎፋ ዞን ፋይናንስና ፕላን መምሪያ በዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ሥር የሚገኙ የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን እንደሚከተለው በሎት የተከፋፈሉትን በሚገኙበት ቦታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
|
ምድብ (ሎት) |
የተሸከርካሪው ዓይነት |
ዝርዝር መረጃዎች |
ምርመራ |
|
ሎት1 |
ASIA STAR 60 SAT BUS |
|
ስኮርት ጎማን ጨምሮ ሌሎች መኪናው ለገዛ ከመኪናው ጋር የመጣ ከክሪክ ውጭ ሁለት ማዳበርያ ሙሉ መለዋወጫ ዕቃ ያለው አውቶብስ፡– |
|
ሎት 2 |
ኒሳን ኮብራ |
ዝርዝር መረጃውን ዋጋ ሙያ ላይ ይመልከቱ |
|
|
ሎት 3 |
ሀይሉክስ |
ዝርዝር መረጃውን ዋጋ ሙያ ላይ ይመልከቱ |
|
|
ሎት 4 |
ሲንግል ጋቢና ፒካፕ |
ዝርዝር መረጃውን ዋጋ ሙያ ላይ ይመልከቱ |
|
|
ሎት 5 |
ኒሳን ፓትሮል |
ዝርዝር መረጃውን ዋጋ ሙያ ላይ ይመልከቱ |
|
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 የስራ ቀናቶች ከጠዋቱ 03:00 እስከ 10፡00 ድረስ በጎፋ ዞን ፋይናንስና ፕላን መምሪያ ግቢ በመገኘት ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ ሰነድ የማይመለስ 500 ብር፣ ብቻ በመክፈል መግዛት ይኖርባቸዋል፣
- ተጫራቾች ለሎት 1 ለአውቶብሱ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ ብር እና ከሎት 2 እስከ 5 ድረስ ላሉት ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ብቻ የጨረታ ማስከበርያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ተሞልቶ ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
- ተጫራቾች ተሸከርካሪዎች ጎፋ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ግቢ ባለሙያ ይዘው በመሄድ መመልከት ይችላሉ፣
- ተጫራቾች ከጨረታ ሰነድ ጋር በተያያዘ የዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ላይ ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ ሲሞሉ በተጨማሪነት ስማቸውንና አድራሻቸውን ማለትም ከልላቸውን፣ ዞናቸውን፣ ወረዳቸውን፣ ከተማቸውን፣ ክፍለከተማ፣ የቤት ቁጥራቸውንና የስልክ ቁጥራቸውን በግልጽ በመጻፍ በመፈረም ማቅረብ ግዴታ አለባቸው፣
- ከጨረታ መዝጊያ ሠዓት በኋላ የሚደርሱ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸው ተቀባይነት የለውም፣
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የጨረታ ማስታወቂያው በግልጽ ከመጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን የጨረታ ሣጥኑ በ16ኛው ቀን 3:00 ሰዓት ታሽጎ 3:30 ላይ ጨረታው ይከፈታል። 16ኛው ቀን ቅዳሜና ዕሁድ ወይም በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል፣
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፈበትን ገንዙበ የጨረታ አሸናፊ መሆናችሁ በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን አንስቶ በ30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፋትን አጠቃላይ ዋጋ ከፍሎ ዕቃውን የማንሳት ግዴታ አለባቸው ይህ ካልሆነ የጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት CPO የሚወረስ ይሆናል፣
- ለተሽከርካሪ የስም ማዛወሪያ ወጭዎች፣ ከቦታ ለማንሳት የሚያስፈልጉ ማንኛውንም ወጪ ሙሉ በሙሉ በዥዎች የሚሸፈን ይሆናል፣
ማሳሰቢያ፦ መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
- የመኪናዎች ዝርዝር መረጃ በጨረታ ዋጋ መሙያ ቅጽ ላይ ማግኘት ይችላሉ፣
- ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0913329728/ 0912455809 ይደውሉ!
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት ጎፋ ዞን ፋይናንስና ፕላን መምሪያ