በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ቁጥር 2 መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Feb 11, 2026)

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ መለያ ቁጥር 02/2018

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ቁጥር 2 መካከለኛ ግብር ከፋዮች //ቤት በተለያዩ ሎቶች

  • የደንብ ልብስ፣
  • የጽህፈት መሳሪያዎች እና አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፣
  • ህትመት ውጤቶች፣
  • የፅዳት እቃዎች፣
  • የቋሚ እና አላቂ የመረጃ ቴክኖሎጂ እቃዎች፣
  • ልዩ ልዩ መሳሪያዎችግዥ፣
  • ለተሽከርካሪዎችና ሌሎች መጓዣዎች እድሳት ጥገናና ጌጣጌጥ ግዥ፣
  • ለፕላን፣
  • ለማሽነሪእና ለተገጣሚዎች እድሳትና ጥገና ለህንፃና ቁሳቁስ እና ለተገጣጣሚዎች እድሳት እና ጥገና፣
  • የጽዳት ሰራተኞች ወይም አውትሶርስ አገልግሎት ግዥ ከነ ጽዳት እቃው፣
  • ለህንፃ፣ ለቁሳቁስለተገጣጣሚዎች መግዣ(ቋሚ እቃዎች መግዣ)
  • ልዩ ልዩ እቃዎች (አበባ እና አበባ ማስቀመጫእንዲሁም ሌሎች) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጸውን መስፈርት የምታሟሉ አቅራቢዎች እንድትሳተፉ ይጋብዛል።

  1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤
  2. የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት (Tin) ያላቸው መሆኑን፤ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ እና መረጃ ያላቸው፤
  3. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡና ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምሥክር ወረቀት ከሰነዳቸው ጋር አያይዘው የሚያቀርቡ፡፡
  4. በአነስተኛና ጥቃቅን የተደራጁ ከሆኑ ከአደራጀው አካል የድጋፍ ደብዳቤ፤
  5. የጨረታ ማስከበሪያ መጠን፡የደንብ ልብስ ሎት አንድ 3,000.00 ለአላቂ የጽህፈት እቃዎች (ሎት2) ብር 1,000.00 ለህትመት ውጤቶች (ሎት3) ብር 2,000.00፣ለጽዳት እቃዎች (ሎት4) ብር 1,000.00፣ልዩ ልዩ የጽህፈት መሳሪያዎች (ሎት5) ብር 3,000.00 ለተሽከርካሪዎችና ሌሎች መጓጓዣዎች እድሳት ጥገናና ጌጣጌጥ ግዥ (ሎት6) ብር1,000.00፣ለፕላን፣ለማሽነሪ እና ለተገጣጣሚዎች እድሳትና ጥገና (ሎት7) ብር1,000፣ለህንጻ እና ለቁሳቁስ መገጣጠሚያዎች ዕቃ ግዥ (ሎት8) ብር 3000.00 ፎቶ ኮፒና ፕሪንተር አገልግሎትና የጥገና ዕቃዎች (ሎት9) ብር2,000.00፣ለህንጻ ለቁሳቁስ ለተገጣጣሚዎች ቋሚ ዕቃዎች ግዢ (ሎት10ብር 3,000.00፣ልዩ ልዩ እቃዎች (ሎት11) ብር 2,000.00 የጽዳት ሰራተኞች ወይም አውት ሶርስ አገልግሎት ግዥ ከነጽዳት እቃው (ሎት 12) ብር 5,000.00 በባንክ በተመሰከረለት (CPO) ብቻ መያዝ አለበት::
  6. ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ሎቶች የእቃው ናሙና ወይም ሳምፕል በድርጅቱ በተረጋገጠ ማህተም እና ፊርማ ከጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት በፊት ለግዥ ከፍል ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ድረስ ስቴዲየም አካባቢ ይሓ ሲቲ ሴንተር ህንፃ 3 ፎቅ ላይ በሚገኘው የቅ//ቤታችን ግዥና ፋይናንስ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 303 መግዛት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የሚጫረቱበት ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦርጅናሉንና ኮፒውን ለብቻ ለብቻ በማድረግ ዘወትር በስራ ቀን እና ሰዓት ጋዜጣው ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት 230 እስከ 1100 እንዲሁም ቅዳሜን 230 እስከ 1100 በዚሁ በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።ጨረታው በ11ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 3 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 303 ግዥና ፋይናንስ ቢሮ ይከፈታል።
  9. የጨረታው አሸናፊ ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ በ10 ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን የእቃው ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት (CPO )በማስያዝ ከመስሪያ ቤቱ ጋር ውል በመፈፀም አሸናፊ የሆነባቸውን እቃዎች በሙሉ //ቤቱ ንብረት ከፍል ድረስ በማምጣት ገቢ ማድረግ አለበት።
  10. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ  የተጠበቀ ነው።
  11. ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0115581772/0115580505 መጠየቅ ይቻላል።

በአዲስ አበባ ከተማ  አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ቁጥር 2 መካከለኛ ግብር ከፋዮች //ቤት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *