Addis Zemen (Apr 22, 2026)
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ምዕ/ኢ/ህ/ክ/መ/ የአንድራቻ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት በወረዳ ውስጥ ለሚገኙት ሴክተር መ/ቤቶች ሥራ አገልግሎት የመውል ኤሌክትሮንክስ መሳሪያዎችን አልኮ ሻንጣ፤ ጀነሬተር እና ሞተር ሳይክል በዘርፉ የተሰማሩትን ህጋዊ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት ተጫራቾች ለጨረታ ብቁ የሚያድርጋቸው፤
- አግባብነት ያለው የታደሰ ንግድ ስራ ፈቃድ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፊኬት የዘመኑን 2018 ዓ.ም ግብር የከፈሉና ፈቃዳቸውን ያሳደሱ ተጫራቾችን ይጋብዛል።
- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ/ በአን/ወ/ገ/ቅ/ጽ/ቤት በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከአን/ወ/ፋይ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ግዥ ንብ/አስ/ር ስራ ሂደት ቢሮ ቁ 11 መረከብ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድና ዋጋ የተሞላበት ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ሰነድ ኦሪጅናልና እያንዳንዱ ሁለት ኮፒ በሰም በታሸገ ፖስታ ማቅረብ የሚችል/ትችል።
- ተጫራቾች 10000 /አስር ሺህ/ብር የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ የክፊያ ማዘዣ/CPO/ማቅረብ የሚችል/ትችል።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 የስራ ቀናት አየር ላይ ይቆያል።
- ጨረታው በ22ኛ ሥራ ቀን በጧቱ 3.00 /ሶስት/ሰዓት ላይ ታሽጎ በዕለቱ ከጠዋቱ 4፡30/አራት ሰዓት ተኩል ላይ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ካልሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ይከፈታል።
ማሳሰቢያ፡–
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨርታውን ሙሉበሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- በጨረታ ከፈታ ወቅት ተጫራቾች ወይንም ወኪሎቻቸው ያለመገኘት ጨረታውን አያስተጓጉልም።
- ለበለጠ ማብራሪያ አን/ወ/ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት ግዥ ንብ/አስ/ር ሥራ ሂደት መጠየቅ ይቻላል።
በደ/ምዕ/ኢ/ህ/ክ/መ/ የአድራቻ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ጽ/ቤት