Reporter (Apr 22, 2026)
በሙጪ ኦዲተሮች ሂሳብ ለማስመርመር
በድጋሜ የወጣ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ሰነድ ቁጥር 0014/2018
ዘመን ኢንሹራንስ አ.ማ ሂሳብ ለማስመርመር የውጭ ኦዲተሮችን አወዳድሮ ለሶስት አመት ማለትም እ.ኢ.አ ከ2026 እስከ 2028 የተሰሩ የኩባንያዉ ሒሳቦችን ውል በመግባት ማሰራት ይፈልጋል::
በመሆኑም ከዚህ በታች በተዘረዘረው መስፈርት መሰረት የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንድትሳተፉ እየገለጽን፡–
1. ተጫራቾች ጨረታውን ለመሳተፍ በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸዉ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢየሆኑ የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፤ቲን ሰርተፊኬት እና ታክስ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸዉ::
2. ተጫራቾች ከፈቃድ ሰጪው አካል ኩባንያችንን መመርመር የሚያስችል ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው::
3. ተጫራቾች ከኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸዉ::
4. ተጫራቾች ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ተቋማትን የመረመሩ ቢሆን ይመረጣል::
5. የ “IFRS” ሰርቲፋይድ የሆነ እና በ “IFRS” ኦዲት ሰርቶ የሚያውቅና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል::
6. ተጫራቾች ከዚህ ቀደም ከሠሩባቸው መ/ቤቶች ለሠሩበት ምስክርነት የሚሠጡ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማስረጃዎችን ማቅረብ ይኖርባቸዋል::
7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ 50,000(ሃምሳ ሺህ)ብር በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ማስያዝ ይኖርበታል::
8. ተጫራቾች ስርዝ ድልዝ የሌለው ጠቅላላ ዋጋቸውን (ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በማያያዝ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል በኦርጂናል እና በኮፒ በፖስታ በማሸግ በጨረታ ሣጥን ውስጥ ዋናው መ/ቤት 5ኛ ፎቅ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
9. የጨረታው አሸናፊዎች እንደታወቀ ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያውኑ ተመላሽ ይደረጋል::
10. የጨረታ አሸናፊ መሆኑን እንደተገለፀለት በአምስት ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% (10 መቶኛ) የውል ማስከበሪያ በማስያዝ የስምምነቱን ውል ይፈርማል::
11. የጨረታው አሸናፊ ውል ከተፈራረመ በኋላ በተያዘው የጊዜ ገደብ ስራቸውን አጠናቀው የመጨረሻ የኦዲት ሪፖርት እንዳቀረቡ የሰሩበት ክፍያ በውሉ መሰረት ከጨረሰ እና የውሉ ጊዜ ሲያበቃ ያስያዘው ውል ማስከበሪያ ተመላሽ ይደረጋል::
12. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከሚያዚያ 14/2018ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት በ 6ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ከዘመን ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን::
13. ጨረታው በ7ኛው ቀን ሚያዚያ 19/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት ተጫራቾቹ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ባይገኙም ከጠዋቱ 4፡30 የሚከፈት ይሆናል::
14. ኩባንያው ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ፡ ቦሌ አለም ህንፃ 5ኛ ፎቅ.
ስልክ ቁጥር 0116 151 493 / 0115 575 850
አ/አበባ