Yedebub Nigat (Apr 18, 2026)
በድጋሚ የመሬት ሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን በዲላ ከተማ አስተዳደር መምሪያ ለመኖሪያ፣ለንግድ(ሆቴል) አገልግሎት የሚውል መሬት አዘጋጅቶ በሊዝ ጨረታ ለማስተላለፍ ይፈልጋል።
በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ተጫራቾች በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በዲላ ከተማ አስተዳደር መሬት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ቁጥር 2 በመቅረብ የማይመለስ ለመኖሪያ 300 (ሶስት መቶ ብር) እና ለንግድ 400(አራት መቶ ብር) በመክፈል ሰነዱን መግዛት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ በተጨማሪም የጨረታው ሳጥን ላይ የጨረታውን ሰነድ የማስገባት ሂደት በ10ኛው የሥራ ቀን ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ተጠናቆ በ11፡00 ሰዓት ታዛቢዎች ባሉበት ታሸጎ በ11ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ህጋዊ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት መሆኑን እንገልጻለን።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ፕላን ል/መምሪያ