Reporter (Apr 29, 2026)
የኦዲት ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ እውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማኅበር ሀገረ በቀል በጎ አድራጎት ለመጪው 3 ዓመታት የማህበሩን አመታዊ የሂሳብ ምርመራ በውጪ ኦዲተሮች ማስደረግ ይፈልጋል።
ማለትም
1. እ.ኤ.አ ከ July 1/2025 – June 30/2026
2. እ.ኤ.አ ከ July 1/2026 – June 30/2027
3. እ.ኤ.አ ከ July 1/2027 – June 30/2028
በመሆኑም የሒሳብ ምርመራውን ለማከናወን የሚፈልግ የኦዲት ድርጅት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 የሥራ ቀናት የሒሳብ ምርመራውን ለማከናወን የሚገባውን ዋጋ እና ሥራውን ለመጨረስ የሚፈጀወን ቀን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማህበሩ ፅ/ቤት እንዲቀርብ እየጠየቅን በተጨማሪ ተወዳዳሪው የኦዲት ድርጅት የሚከተሉትን ዶክመንቶች አሟልቶ መወዳደር ይጠበቅበታል።
1. የሙያ ማረጋገጫ
2. የታደሰ ንግድ ፈቃድ
3. የዘመኑን ግብር መክፈሉን የሚያሳይ ማረጋገጫ
4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት
5. ከፌደራል ኦዲት መስሪያ ቤት ለበጀት አመቱ የታደሰ ፈቃድ
6. ከላይ የተቀሱትን አመታት በሙሉ በPSAS Accounting System ሪፖርቱን ማቅረብ የሚችል
7. AABE ፈቃድ ያለው
እንዲሁም ተጨማሪ የሂሳብ ሰነዶችንና መረጃዎችን ከዚህ በታች በተገለፀ የማህበሩ አድራሻ በሥራ ሰዓት መወዳደር ትችላላችሁ።
አድራሻ:- ቃሊቲ ውሃ ልማት ወርድ ብሎ በርታ ኮንስትራከሽ ግቢ ውስጥ
በአካል በመቅረብ እንዲሁም በሞባይል ቁጥር 09 11-15-13-41 ወይም 09 30-28-94-14 አስፈላጊውን መረጃ በመጠየቅ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። የቦክስ ፋይል ብዛት ቢበዛ 3 ነው።