Addis Zemen (May 10, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 06/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ዞን ለሚገኙ ሴከተር መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ 50 ሲሲ ሞተር ሳይክሎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል::
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መወዳደር ትችላላችሁ:
- ተጫራቾች ህጋዊና የዘመኑ የታደሰ ወይም አዲስ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
- የታክስ ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው፣
- የአቅራቢነት የምዝገባ ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የግዢው መጠን ከብር 500,000/ አምስት መቶ ሺህ ብር ብቻ/ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ/VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-5 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻቸው ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን እቃ አይነት፣ የአምራቹን ስምና የተመረተበት ዓ.ም በዝርዝር ከዋናው ሰነድ ጋር ማያያዝ አለባቸው፡፡
- ለሚወዳደሩባቸው እቃዎች ናሙና ሲጠየቁ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 30,000/ሰላሳ ሺህ ብር ብቻ/ በባንከ በተመሰከረለት CPO ወይም ቢድ ቦንድ ለ9ዐ ቀናት የሚቆይ/ በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ስም ተዘጋጅቶ ከኦርጂናል ዶክመንት ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል::
- ተጫራቾች ለጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት ጀምሮ ዘወትር በስራ ቀናት የማይመለስ ለእያንዳንዳቸው ብር 100/አንድ መቶ ብር ብቻ/ ለጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ በመከፈል ሰነዱን ከጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥ ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ::
- ተጫራቾች አንድ ኦሪጅናል እና አንድ ኮፒ ዶክመንት በአንድ ትልቅ እናት ፖስታ በሰም በማሸግ እስከ 16ኛው ቀን 6፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡ዐዐ ሰዓት የጨረታ ሰነድ ያለበትን ሳጥን ታሽጐ በዚሁ እለት ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ አዳራሽ በይፋ ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ተጫራች ማሸነፉ እንደተገለፀለት በውሉ መሠረት ዕቃዎቹን ጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፡፡
- መ/ቤቱ በጨረታው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡–
ለበለጠ መረጃ መ/ቤቱ ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0113300112 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፣
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘዋወራል፡፡
- በጨረታው ሂደት ውስጥ ተሻሽሎ የወጣው አዲሱ የክልሉ የግዢ መመሪያ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ