የጎጃም ልማት ማኅበር የ2018 የበጀት ዓመት ሒሳቡን ማስመርመር ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የጎጃም ልማት ማኅበር የ2018 የበጀት ዓመት ሒሳቡን ማስመርመር ይፈልጋል


Reporter (May 10, 2026)

የኦዲት ሥራ ማስታወቂያ

የጎጃም ልማት ማኅበር በኢፌዲሪ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ደንብና መመሪያዎችን መሠረት የተቋቋመ ነው:: ማኅበሩ የ2018 የበጀት ዓመት ሒሳቡን ማስመርመር ይፈልጋል:: ስለዚህ ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ የኦዲት አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች መወዳደር ይችላሉ።

መስፈርቶች

1. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣

2. በሙያው ብቃት ያላቸው ለመሆኑ በመንግስት የተመዘገቡ፣

3. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆኑ መረጃ የሚያቀርቡ፣

4. ቢያንስ ለ5 ዓመታት በሙያው የሠሩ፣

5. የታክስ መለያ ቁጥር (Tin Number) ያላቸው::

ከላይ የተጠቀሱ መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎች የቴክኒክ እና ፋይናንስ ፕሮፖዛላቸው ውስጥ ሥራው ተጠናቆ ርክክብ የሚያደርግበትን ጊዜ እና ለአገልግሎቱ የሚቀርበው ዋጋ ማካተት ይኖርበታል። ሥራው የሚጀምረው የበጀት ዓመቱ ከተጠናቀቀ 6ኛው ቀን ጀምሮ ይሆናል። ተወዳዳሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን መመዘኛ መረጃዎች የካተተ ፕሮፖዛል በታሸገ ፖስታ በማዘጋጀት ማስታወቂያው ከወጣበት ከ15 ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት በቂርቆስ ክ/ከ/ማ ወረዳ 04 የቤት ቁጥር 287 የድሮው ቡልጋሪያ ኢምባሲ ጎን በሚገኘው የልማት ማኅበሩ ጽ/ቤት በማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ያስታውቃሉ።


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *