Addis Zemen (May 12, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር BNCO/001/08/2018
ብርሃን ናትና የበጎ አድራጎት ድርጅት በሕጋዊ የውጭ ኦዲቶሮች የድርጅቱን የአንድ ዓመት ኦዲት ለማድረግ ስለፈለገ ሕጋዊ ፍቃድ ያላቸዉ ተወዳዳሪዎች የቴክኒካልና የፋይናንስ ሁለት የተለያዩ ፕሮፖዛል በማቅረብ በግልፅ ጨረታ ለማወዳደር ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት ተወዳዳሪዎች ማሟላት ያለባቸው፡–
1. በውጭ ኦዲት ሞያ ሕጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ ቲን ነምበር፣ ቫት ተመዝጋቢ መሆኑንና ሌሎች አስፈላጊ ዶክመንት የሚያቀርብ
2. የጨረታ ሰነዱን ከብርሃን ናትና በጎ አድራጎት ድርጅት ቢሮ ከትግራይ ክልል አክሱም ከተማ መውሰድ የሚችል
3. ሁለት የጨረታ ፕሮፖዛል ሊያቀርብ የሚችል ሁኖ አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ ቴክኒካል ፕሮፖዛል እንዲሁም አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ ፋይናንስ ፕሮፖዛል ሁለቱም በተለያየ ፖስታ በስርዓት ታሽጎ ማህተም ያረፈበት መሆን አለበት
4. የጨረታው ግምገማ መጀመሪያ ቴክኒካል ፕሮፖዛል የሚታይ ሁኖ ዝቅተኛውን መስፈርት ያሟላ ተወዳዳሪ የፋይናንስ ፕሮፖዛሉ ተከፍቶ ይታያል ሆኖም ግን ዝቅተኛ የቴክኒካል መስፈርት ያላሟላ ተወዳዳሪ የፋይናንስ ፕሮፖዛል አይከፈትም
5. ቴክኒካል ፕሮፖዛል ተወዳዳሪዎች በአካል ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ11 ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ይከፈታል
6. የጨረታ ሰነዱ በአማርኛ ወይም በኢንግሊዘኛ መቅረብ ይችላል
7. ጨረታው የሚከፈተው የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ከ10 የሥራ ቀን በኋላ ባለው ቀጣይ የሥራ ቀን ሆኖ በጨረታ ሰነድ በተገለፀው ቀንና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል እንዲሁም የሚከፈተው በአክሱም ከተማ የድርጅቱ ዋና ቢሮ መሆኑን እናሳውቃለን።
8. ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ሳይገኙ በመቅረታቸው የጨረታውን መከፈት አያስተጓጉልም።
9. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
ለተጨማሪ መረጃ፡– በስልክ ቁጥር 09 14 76 41 45 / 09 11 70 95 22 ደውለው ይጠይቁ
ብርሃን ናትና የበጎ አድራጎት ድርጅት