የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት መልካዲዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተለያዩ ዕቃዎች (ላፕቶፕ እና ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ፐሪንተሮች፣ የማባዣ ማሽኖች፣ ቴሌቪዝኖች፣ የተለያዩ የዉሃ እቃዎች፣ የግንባታ እቃዎች እና ሌሎችም ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል – test3.diretenders.com

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት መልካዲዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተለያዩ ዕቃዎች (ላፕቶፕ እና ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ፐሪንተሮች፣ የማባዣ ማሽኖች፣ ቴሌቪዝኖች፣ የተለያዩ የዉሃ እቃዎች፣ የግንባታ እቃዎች እና ሌሎችም ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል


Addis Zemen (May 24, 2026)

በድጋሚ የወጣ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር፡- መልካዲዳ/ስተ/002/2018

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት መልካዲዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙትን

  • የተለያዩ ዕቃዎች
  • (ላፕቶፕ እና ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ፐሪንተሮች፣ የማባዣ ማሽኖች፣ 
  • ቴሌቪዝኖች፣
  • የተለያዩ የዉሃ እቃዎች፣
  • የግንባታ እቃዎች እና ሌሎችም ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

 በመሆኑም የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ በድጋሚ ባወጣው የዕቃዎች ሽያጭ ጨረታ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች።

  1. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የሽያጭ ጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል መልካዲዳ በሚገኘው የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት መልካዲዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ ፋይናንስ ቢሮ በመገኘት እና ክፍያ በመፈጸም ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ከግንቦት 17/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል።
  2. በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚያቀርቡትን አጠቃላይ ዋጋ 2% ለስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት/Refugees and Returnees Service /በሚል የተዘጋጀ የክፍያ ማዘዣ /CPO/ የባንከ ዋስትና /Bank Gurantee/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  3. ማንኛውም ተጫራች ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት መልካዲዳ በሚገኘው የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ መልካዲዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ በመገኘት ዕቃዎቹን መመልከት/መጎብኘት ይችላል።
  4. ጨረታው መልካዲዳ በሚገኘው የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ መልካዲዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ የሚካሄድ ሲሆን የጨረታው ሳጥን ግንቦት 28 ከቀኑ 8፡30 ታሽጎ በዕለቱ ግንቦት 28 ከቀኑ 9፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል።
  5. የጨረታ አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ውሰጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
  6. ተጫራቾች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ወይም በማስታወቂያ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ያሸነፉትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ዕቃዎችን መረከብ አለባቸው።
  7. በተራ ቁጥር 6 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረገ ተጫራች ለጨረታው ማስከበርያ ያስያዘው ሲፒኦ ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ገቢ በማድረግ የተሻለውን አማራጭ የመውሰድ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  8. አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  9. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር +251912487328 ወይም +251912189068 ደውሎ መጠየቅ ይችላል።

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት መልካዲዳ

ቅርንጫፍ ጽ/ቤት